በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወርቅነህ ገበየሁ የሚመራ የልዑካን ቡድን ከረቡዕ ሚያዝያ 11 ቀን 2009 ዓ.ም. ጀምሮ በግብፅ ይፋዊ ጉብኝት እንደሚያደርግ ተገለጸ፡፡
ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት ለሪፖርተር የተላከው መግለጫ እንደሚያመለክተው፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጉብኝቱን የሚያደርጉት ከግብፅ አቻቸው ሳሜህ ሹክሪ በተደረገላቸው ግብዣ መሠረት እንደሆነ ታውቋል፡፡
ኢትዮጵያ ታላቁን የህዳሴ ግድብ መገንባት ከጀመረች አንስቶ የሁለቱም አገሮች ግንኙነት አወዛጋቢ ጉዳዮች እየገጠሙት ሲሆን፣ ሱዳንን ጨምሮ በግድቡ ላይ የሚካሄደው የሦስትዮሽ ምክክር አሁንም ድረስ አልተጠናቀቀም፡፡ ሚኒስትሩ ከግብፅ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር የሁለትዮሽ ውይይት እንዲያደርጉ መታወቁን የማነ ናግሽ ዘግቧል፡፡
Standard (Image)
No comments:
Post a Comment