Tuesday, April 11, 2017

በወላይታ የኃይለማርያም ደሳለኝ የትውልድ ቦታ ትልቅ የገበያ ማዕከል በእሳት ወደመ

(ዘ-ሐበሻ) መነሻው ባልታወቀ ሁኔታ አንድ ትልቅ የገበያ ማዕከል በደቡብ ክልል በወላይታ አረካ ከተማ ውስጥ መውደሙ ተሰማ:: ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው መንግስት የአንድን ወገን የሚጠቅም ኢኮኖሚና አስተዳደር በአካባቢው በማስፈኑ ሕዝቡ በንዴት ሳያነዳው እንዳልቀረ ነው::
የአካባቢው ነዋሪዎች ለዘ-ሐበሻ በላኩት መረጃ እንደገለጹት ዛሬ በአረካ የወደመው ትልቅ የገበያ ማዕከል በደህዴን ካድሬዎችና በሕወሓት ደጋፊዎች የተያዙ ናቸው::
የ እሳት መነሻው ከመንግስት በኩል የተሰጠ ምንም ዓይነት ምክንያት ባይኖርም ንግድ ድርጅቶቹ ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል መልኩ እንደወደሙ መረጃዎች ጠቁመዋል:: ኃይለማርያም ደሳለኝ በሕወሓት መንግስት ምርጫ ወቅት በዚሁ አረካ ከተማ 100% አሸንፈዋል መባሉ የሚታወስ ሲሆን ዛሬ እርሳቸውን በሚቃወሙ ሰዎች ይህ የገበያ ማዕከል ወደመ መባሉ የፖለቲካውን ኪሳራ ያሳያል የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች አሉ:: የአረካ ነዋሪዎች የበይ ተመልካች ሆንን በማለት ደህዴንን እና ኃይለማርያም ደሳለኝን እንደሚያማርሩ ጨምሮ የደረሰን መረጃ ይጠቁማል::

No comments:

Post a Comment