Sunday, April 9, 2017

አርበኞች ግንቦት 7 በፈጸመው ጥቃት በጥበቃ ሥራ ላይ የነበረ ምክትል ጋንታ መገደሉ ተዘገበ

ትንሳኤ ራድዮ እንደዘገበው መጋቢት 28 ቀን 2009 ዓ/ም በሰሜን ጎንደር እና በደቡብ ጎንደር መሀከል በምትገኘው ልዩ ቦታው ግም ውሃ ከተባለው ሥፍራ ላይ ከለሊት 6፡ ሰዓት ሲሆን በጥበቃ ላይ በነበሩ የወያኔ ወታደሮች ላይ የአርበኞች ግንቦት ታጋዬች ድንገተኛ ጥቃት በመፈፀም በዕለቱ በጥበቃ ሥራ ላይ የነበረ ምክትል ጋንታ መሪን መግደላቸው ተገልጾአል።
File Photo
በዚህ ጥቃት ህይወቱ ሊያልፍ የቻለው ጋንታ መሪ ስም ሳጅን ደረጀ አማረ የሚባል ሲሆን ሟች በጥይት ከተመታ ቦኋላ ህይወቱን ለማትረፍ ወደ ጎን ሆስፒታል ተወስዶ የነበረና ነገር ግን በደረሰበት ከፍተኛ ምት ሂይወቱ ሆስፒታል እንደደረሰ ማ ተገልጾአል። የሳጂን ደረጀ አማረ አስከሬን ትናንት መጋቢት 29 ቀን ወደ ትውልድ ቦታው ፎገራ ወረዳ ወረታ ተወስዶ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ ተፈጽሟል ተብሏል። አርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮች በወሰደው በዚህ ጥቃት ከፍተኛ የመቁሰል አደጋ የደረሰበት አወቀ የተባለ የሚሊሺያ ኮማንደር ሁለት እግሮቹን ተመቶ ጎንደር ሆስፒታል ተኝቶ በመታከም ላይ እንደሚገኝ ታውቆአል።

No comments:

Post a Comment