Friday, October 27, 2017

አቶ ኃይለማርያም መንግስት የአባ ዱላ ገመዳን የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ እየመረመረው ነው አለ source zehabesha


ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ አቶ አባዳላ ገመዳ ያቀረቡትን የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ እየመረመረው ይገኛል አሉ፡፡ በተቃራኒው ደግሞ አቶ በረከት ስምዖን ያቀረቡትን የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ መንግስት እንደተቀበላቸው ተናግረዋል፡፡ በዛሬው ዕለት በኢህአዴግ ፓርላማ ተገኝተው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እሳቸው በተገኙበት የአዲስ አፈ ጉባኤ ምርጫ ይካሔዳል ተብሎ ተጠብቆ ነበር፡፡ ሆኖም ባልታወቀ ምክንያት ምርጫው እንዲራዘም ተደርጓል፡፡
አፈ ጉባኤ አባዱላ ገመዳ የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ ያስገቡት ከአቶ በረከት ስምዖን ቀደም ብለው ቢሆንም፣ የእሳቸው ጉዳይ ተቀምጦ የአቶ በረከት ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቷል ተብሏል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለዚህ እንደ ምክንያት የሰጡት ደግሞ፣ አቶ በረከት ከዚህ ቀደምም ተደጋጋሚ የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ ማቅረባቸውን ነው፡፡ የአባ ዱላ የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ ግን የመጀመሪያው በመሆኑ፣ መንግስት እየመረመረው ወይም እየመከረበት ይገኛል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
አቶ አባዱላ ገመዳ የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ ያቀረብኩት ‹‹የህዝቤ እና የድርጅቴ ጥቅም ስለተነካ ነው፡፡›› ማለታቸው አይዘነጋም፡፡ አቶ አባዱላ ገመዳ አሁንም በስራቸው ላይ የሚገኙ ሲሆን፣ ከመቼ ጀምሮ ከስራቸው እንደሚሰናበቱ የታወቀ ነገር የለም፡፡ መንግስት ያቀረቡትን ጥያቄ መርምሮ መቼ ምላሽ እንደሚሰጣቸውም ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም የገለጹት ነገር የለም፡፡ በአሁን ሰዓት በገዥው ፓርቲ ውስጥ ከፍተኛ መከፋፈል የተፈጠረ ሲሆን፣ አለመደማመጥ መስፈኑም እየተገለጸ

No comments:

Post a Comment