Monday, October 16, 2017

አባዱላ ገመዳ የለቀቁበትን ምክንያት በዝርዝር አስረዱ source zehabesha

ምክንያት በዝርዝር አስረዱ
 



ከላይ በቀረበው የአባዱላ ንግግር ላይ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሸፈራው የሚከተለውን ምላሽ ሰጥቷል::
ስለ ኦህዴድ ብዙ ብዙ እየተባለ ነው። አባዱላ የህዝብና ድርጅት ክብር ስለተነካ ለቅቄያለሁ ብሏል። በመሰረቱ የህዝብ ክብር አሁን አይደለም የተነካው። ብዙ ሳንርቅ በ2008 እነ አባይ ፀሃዬ፣ እነ ጌታቸው ረዳ በህዝብ ላይ ምራቅ ሲረጩ እነ አባዱላ ጭጭ ብለው ነበር። ዛሬ ነቃን፣ መረረን፣ በዛ ካሉም መልካም ነው።
በ2008 የተነሳው ህዝባዊ ንቅናቄ ትንፋሽ ሲያሳጣቸው ሚዲያውን መግለጫ በመግለጫ አድርገውት ነበር። በዋነኛነት ችግሩ የህዝብ ሳይሆን የኢህአዴግ ነው ብለዋል። ይህን ብለው ግን በዚሁ ንቅናቄ ሰበብ የታሰሩትን አልፈቱም። እንዲያውም የሀሰት ክስ ቀርቦባቸዋል። የኢህአዴግ ችግር ነው በተባለው ጉዳይ የሀሰት ክስ ከቀረበባቸው መካከል እነ አቶ በቀለ ይገኙበታል!
እነ አቶ በቀለ የቀረበባቸውን የሀሰት ክስ ተከላከሉ ተብለው ለጥቅምት 27፣ 28 እና 29 ቀጠሮ ተይዟል። ለዚህ የሀሰት ክስ በምስክርነት የጠሩት ደግሞ ችግሩ የህዝብ ሳይሆን የእኛ ነው ብለው ህዝብን ይቅርታ የጠየቁትን እነ አባዱላ ገመዳ እና እነ ለማ መገርሳን ነው!
እነ አቶ በቀለ የተከሰሱት እነ አባዱላ ገመዳ ክብሩ ተነክቷል ያሉትን ህዝብ አነሳስታችሁዋል፣ አሳምፃችሁዋል ተብለው ነው። ጥቅምት27፣ 28ና 29 እነ በቀለ የሚያስመሰክሩት ለራሳቸው ብቻ ሳይሆን በገዥዎቹ ስለተፈረጀው፣ ሽብር፣ አመፅ ፈጥሯል ተብሎ ለሚከሰሰው፣ አሁንም በየ ፍርድ ቤቱ ስሙ ሲነሳና ክብሩ ሲነካ ለሚውለው ህዝብ ነው!
እውነት እነ አባዱላ ፣ እነ ለማ ስለ ህዝብ ክብር ካሰቡ ጥቅምት 27፣ 28ና 29 ፍርድ ቤት ቀርበው እውነታውን፣ ቢያንስ ያኔ መግለጫው ላይ የሰጡትን ቃል ማስረዳት ይጠበቅባቸዋል! ባለስልጣናት በምስክርነት ተጠርተው የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተልኮላቸዋል ተብሎ ያልቀረቡበት ጊዜ አለ።
ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያው ብዙ ለተባለላቸው የኦህዴድ ፖለቲከኞች ጥቅምት 27፣ 28ና 29 ከባድ ፈተና ይገጥማቸዋል! የመጀመርያው ለምስክርነት መቅረብ አለመቅረባቸው ነው! አይቀርቡም እንጅ ከቀረቡ ለመስቀለኛ ጥያቄው ከአሁኑ ፀሎት፣ ምህላ ማስደረግ ይጠበቅባቸዋል! ምክንያቱም ምስክርነቱ ከህዝብ ወይንም ከትህነግ ጋር እንደሚያቀያይማቸው እሙን ነው!

No comments:

Post a Comment