Tuesday, May 9, 2017

የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ገበሬዎች የተገፈፉትን መሣሪያ አስመለሱ

ከሙሉቀን ተስፋው
በሰሜን ሸዋ ዞን በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ መልካ ጅሎ አሞራ ቤት በተባለው አካባቢ የአገዛዙ ወታደሮች ሚያዚያ 16 ቀን 2009 ዓ.ም በአልታሰበ ሰዐት መጥተው 27 የክላሽንኮፍ መሣሪያዎችን መግፈፋቸው የሚታወስ ነው፡፡ የመሣሪያ ገፈፋው ከፍተኛ የሆነ የገበሬዎችን ቁጣ ቀስቅሶ ገበሬዎቹ ለወረዳው አስተዳደርና ለኮማንድ ፖስቱ መሣሪያቸው በአስቸኳይ ካልተመለሰ እርምጃ እንደሚወስዱ ከአስጠነቀቁ በኋላ የወረዳው አስተዳዳሪዎች አፋጣኝ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
በሽማግሌዎች ድርድር ከተደረገ በኋላ ሃያ ሰባቱም ክላሽንኮፎች ሚያዚያ 27 ቀን 2009 ዓ.ም. ተመልሰውላቸዋል፡፡ ከተወሰደው ጥይት የጎደለ ስለነበር ከ600 ብር ካሣ ጋር ተቀብለናል ብለውናል፡፡

* የስልክዎ ባትሪ ቶሎ እያለቀ ተቸግረዋል? – መፍትሄውን ለማየት እዚህ ይጫኑ

ቴዎድሮስ አድሃኖም እና የጎደለው ብር… ለማየት እዚህ ይጫኑ

* የሁለቱ ጀነራሎች ወግ… ለማየት እዚህይጫኑ

No comments:

Post a Comment