Friday, February 3, 2017

አርበኛ አብሲቴ – ኄኖክ የሺጥ



አርበኛ አብሲቴ – ኄኖክ የሺጥላ
ሃሳብን መሞገት ሲዳግት ፥ ቀዳዳ ፈልጎ ትንኮሳ አንዳች ለውጥ አያመጣም ። ለምሳሌ ብርሃኑ ነጋ አብሲት እንደሚጥል ተናግሯል ። አብሲት መጣሉ ወንጀል አይደለም ። ከይህ በፊት እንዳልኩት ለጦሩ ሚንስ ቤት ሁነኛ ሰው ሆኖ ሊሰራ ይችላል። አብሲት በመጣሉ አርበኛ አብሲቴ አላልኩትም ! ቢሳካለትም ባይሳካለትም ያው አርበኛ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ነው የሚባለው። እኔ የተቃወምኩት ስለ አብሲት ያወራበት ሰዓት ጎንደር ውስጥ ሰዉ ትንቅንቅ ላይ በነበረበት ወቅት ነው ! ጎጃም ውስጥ አማሮች ወገኖቻችን ከወያኔ ጋር እየተፋለሙ ባሉበት ወቅት ነው ነው ! ይህንን በመቃወሜ ሙቅ ስለማሞቅ ተከታዮቻቸውን ፥ አልፎ ተርፎ እዚህ ካልፎርኒያ በኪኒን የሚኖሩ በሽተኞችን ሳይቀር እየደጎሙ ፥ ከኔ አልፎ ልጆቼን እና ባለቤትን ፀያፍ በሆነ ቃል ያሰድባሉ። እነሱ ከደሙ ንፁ ለመምሰል ይሞክራሉ ! ዋናው ነገር ግንቦት ሰባቶች እንዴት እንደሚሰሩ አውቃለሁ።
ለምሳሌ እዚህ ሳን ሆዜ የሚኖር አንድ ሃብታሙ የሚባል የኢሃፓ አባል በፅሁፍ ስለተቃወማቸው ብቻ ፥ ይህንን ሰው ከስራው ለማባረር መስራቤቱ ድረስ ደውለው አመልክተዋል ። ይህ ሰው ልጆች አሉት ፥ የዚህ ሰው ከስራ መባረር ልጆቹን ጎዳና ላይ እንዲጥል ያደርገዋል ። በወቅቱ ህንን ለማድረግ ሲያስቡ « እናንተ አብዳችኋል እንዴ ? » ብዬ ተቃውሜያቸው ነበር ። ሃሳቡን ስለገለጠ ከስራ ይባረር ማለት ከወያኔነት በምን ይለያል ? እነዚሁ ሰዎች ቤ/ክ በራፍ ላይ አስተናጋጅ ሆነው ፥ ገቢ ወጪውን ሰላምታ ሲሰጡ ይውላሉ ! አውሬዎች ስለሆነ አምላክ እንኳ የላቸውም !
በመጨረሻ
እኔ መሪ ነኝ አላልኩም ! ስለዚህ መሪ ነኝ ብሎ ስለ ሃብሲት መጣል የሚያወራውን እተቸዋለሁ! እቃወመዋለሁ ! ምክንያቴ ደሞ አላማውን የሳተ ስለመሰለኝ ! ያም ቢሆን አሁንም አርበኛ እብሲቴ ለማለት ግን አልደፍርም ! ነውር ስለሆነ !
እንዲያ ብናየው ጥሩ ነው !
ኄኖክ የሺጥላ

No comments:

Post a Comment