Friday, September 15, 2017

የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል ጥቃት አሁንም እንደቀጠለ ነው source zhebsha

የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል በኦሮሞ ተወላጆች ላይ እየፈጸመ ያለው ጥቃት አሁንም ተጠናክሮ መቀጠሉ ታወቀ፡፡ ከተለያዩ የኦሮሚያ ክፍሎች እየወጡ ያሉ መረጃዎች እንዳመለከቱት፣ በሶማሌ ክልል እና በኦሮሚያ አዋሳኝ ድንበሮች ላይ ከባድ ውጥረት አለ፡፡ ውጥረቱ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መሔዱን የገለጹት የአካባቢው የዓይን እማኞች፣ በተለይ በሶማሌ ክልል የሚኖሩ የኦሮሞ ተወላጆችን የማፈናቀል ድርጊት አሁንም እንደቀጠለ መሆኑን እማኞቹ አክለው ተናግረዋል፡፡

ልዩ ኃይል የተባለው የሶማሌ ክልል ፖሊስ ህወሓት ለክልሉ ፕሬዚዳንት ለአቶ አብዲ በሚሰጠው ቀጥተኛ ትዕዛዝ የሚመራ ሲሆን፣ ልዩ ፖሊሱ በንጹኃን ሰዎች ላይ ግድያ እንዲፈጽም እየተደረገ ያለውም በህወሓት ሴራ ሆን ተብሎ እንደሆነ ምንጮች ይናገራሉ፡፡ ህወሓት በኦሮሞ እና በኢትዮጵያ ሶማሌ ህዝብ መካከል ግጭት እንዳለ በማስመሰል የፖለቲካ ጨዋታ ለመጫወት እየሞከረ መሆኑንም ታዛበዎች ይናገራሉ፡፡ ‹‹ድርጊቱ የከፋፍለህ ግዛ ፖለቲካ ውጤት ነው፡፡›› ያሉት ታዛቢዎቹ፣ ህወሓት በመጨረሻው ሰዓት በሀገሪቱ ላይ የእርስ በእርስ ግጭት እንዲፈጠር እንደሚፈልግም ያክላሉ-ታዛቢዎቹ፡፡

በምስራቅ ኢትዮጵያ ሐረርጌ ልዩ ስሙ ሜኢሶ በተባለው አካባቢ ያለው ውጥረት አሁንም እንደቀጠለ ሲሆን፣ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይልም ደረስ መጣ እያለ ጥቃት እንደሚፈጽም ከአካባቢው የወጡ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ ግጭት ተከስቶባቸዋል በተባሉ የኦሮሚያ እና የሶማሌ ክልል አዋሳኝ ድንበሮች ላይ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ሰፍረዋል ቢባልም፤ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል ግን አሳቻ ሰዓት እየጠበቀ ጥቃት እንደሚፈጽም ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

No comments:

Post a Comment