Tuesday, September 5, 2017

ጀዋር መሐመድ መንግስት በቴዲ አፍሮ ላይ እየወሰደ ያለውን ተደጋጋሚ ክልከላ አወገዘ source zhabesha

(ዘ-ሐበሻ) የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ዳይሬክተር ጀዋር መሐመድ አምባገነኑ የሕወሓት መራሹ መንግስት በቴዲ አፍሮ ላይ በተደጋጋኢ እየወሰደ ያለውን እርምጃ አወገዘ::
“ገዥው አካል ለቴዲ አፍሮ የሚያቀርበውን ትርዒት በተደጋጋሚ በመሰረዙ ተገቢ ያልሆነ እና ኢፍትሃዊ ውሳኔ ነው” ያለው ጀዋር በቴዲ ላይ መንግስት የሚወስደው ክልከላ “ይህ ሁሉ ሀሳብን የመግለጽ ነጻነትን እና ዒላማው የኪነጥበብ ጥቃትን ስለሚያካትት ሁሉም ሊያወግዘው ይገባል” ሲል በፌስቡክ ገጹ ላይ ጽፏል::
ይህ የመንግስት ኪነጠብን የማፈን ተግባር አዲስ ነገር አይደለም አይደለም ያለው ጀዋር “መንግስት ከማንኛውም የህብረተሰብ ክፍል የበለጠ ስነ-ጥበብ እና አርቲስቶችን ይፈራል::” ካለ በኋላ ሥርዓቱ በኦሮሞ አርቲስቶች ላይም ከስልጣን ላይ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የወሰደውን ጥቃት ጠቅሷል::

እንደጀዋር ገለጻ ሕወሓት መራሹ መንግስት ሥልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ ብዙ የኦሮሞ አርቲስቶችን ገድሏል፣ አስሯል እና ከሃገር እንዲሰደዱ አድርጓል::

No comments:

Post a Comment