Friday, September 15, 2017

የህወሓት አጋዚ ወታደሮች ሐረር ውስጥ ግድያ ፈጸሙ source zhebesha

በሐረር የተሰማራው የህወሓት አጋዚ ሰራዊት ግድያ ፈጸመ፡፡ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል በኦሮሞ ተወላጆች ላይ እየፈጸመ ያለውን አሰቃቂ ጥቃት ለመቃወም በሐረር ከትላንት ጀምሮ ህዝባዊ ተቃውሞ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ዛሬም ቀጥሎ የዋለውን የህዝብ ተቃውሞ ተከትሎ የአጋዚ ወታደሮች ወደ ተቃውሞ አቅራቢዎች በቀጥታ በመተኮስ የሰው ህይወት መቅጠፋቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ የሟቾች ቁጥር ምን ያህል እንደሆነ ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ሰዓት ድረስ አልታወቀም፡፡

ከሟቾች በተጨማሪም በጥይት ተመትተው የቆሰሉ ንጹኃን ሰዎች መኖራቸውን የገለጹት መረጃዎች፣ ሐረር በከባድ ውጥረት ውስጥ እንደምትገኝም ተናግረዋል፡፡ በተለይ ሸዋ በር ተብሎ የሚጠራው የሐረር አካባቢ ከፍተኛ የተኩስ ድምጽ ሲሰማ እንደነበር ከዓይን እማኞች ገለጻ ለመረዳት ተችሏል፡፡ እስከ ምሽት ድረስ የቀጠለው የተኩስ ድምጽ ሐረርን የጦርነት ቀጠና እንዳስመሰላት የዓይን እማኞች ተናግረዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል በጅጅጋ ይኖሩ በነበሩ የኦሮሞ ተወላጆች ላይ በፈጸመው ጥቃት ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች ህይወት ተቀጥፏል፡፡ በዛሬው ዕለትም የሟቾች አስከሬን ወደ ሐረር ሲጓጓዝ እንደነበር ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ ትዕዛዝ ከጅጅጋ የተፈናቀሉ የኦሮሞ ተወላጆች ወደ ሐረር እየተወሰዱ ሲሆን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮችም ሐረር ያለመጠለያ እንደሚገኙ ታውቋል፡፡ የትግራይ ነጻ አውጭ ድርጅት የሆነው ህወሓት፣ የሀገሪቱን ህዝብ እርስ በእርስ ለማባላት ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ የገለጹት አስተያየት ሰጪዎች፣ ፈታኝ ጊዜ ላይ በመሆናችን በአንድነት ልንቆም ይገባል ሲሉ አሳስበዋል፡፡
BBN news September 14, 2017

No comments:

Post a Comment