Monday, December 18, 2017

የሶማሌ ክልል ር/መስተዳድር ለተፈናቃዮች ያደረጉት ጥሪ Deutsche Welle (DW) amharic news

በኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ከወራት በፊት አንስቶ ግጭት ተከስቶ እንደነበር ይታወሳል። በሁለቱ ክልሎች መካከል ያለው ወሰን በትክክል ባለመለታየቱ በተነሳው ግጭት በሁለቱም ክልሎች በመቶዎች የሚገመቱ ሰዎች ሕይወት መጥፋቱ እና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩም መፈናቀላችው ይታወቃል።

«ይህ ሁሉ ሰው ሲፈናቀል የፌዴራል መንግሥት የት ነበር?»

በኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች በተከሰተው ግጭት የተፈናቀሉ የኦሮሞ ተወላጆች ወደነበሩበት እንዲመለሱ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አብዲ መሐመድ ኡመር ከጥቂት ቀናት በፊት ጥሪ አቅርበዋል። ተፈናቃዮች ወደ ሶማሌ ክልል እንዲመለሱ የቀረበው ጥሪ በርግጥ ተግባራዊ ሊሆን የሚችል ነው አይደለም፣ እንዲመለሱ የሚያስችሉ ሁኔታዎች አሉ የሉም ፣ እነዚህ ጥያቄዎች ብዙ እያነጋገሩ ነው። በዚሁ ጉዳይ ላይ እኛም ውይይት አካሂደንበታል።
አርያም ተክሌ
ማንተጋፍቶት ስለሺ 

No comments:

Post a Comment