Friday, December 22, 2017

የኦሮምያ ክልል በአ/ አ ከተማ ላይ ያለውን ልዩ ጥቅም በሚመለከት ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የቀረበው ረቂቅ አዋጅ በኦህዴድ አባላት ተቃውሞ ምክንያት ለሌላ ጊዜ ተዛወረ።

የኦሮምያ ክልል በአ/ አ ከተማ ላይ ያለውን ልዩ ጥቅም በሚመለከት ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ የህዝብ አስተያየት ለማሰባሰብ በዛሬው ዕለት የተጠራው ስብሰባ በዋንኛነት በኦህዴድ አባላት ተቃውሞ ምክንያት ለሌላ ጊዜ ተዛወረ።

ዛሬ ጠዋት የፓርላማው የህግና ፍትህ አስተዳደር እና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቋሚ ኮምቴዎች የህዝብ አስተያየት ለማሰባሰብ የጠሩት ሲሆን አብዛኛዎቹ የኦህዴድ አባላት ህዝባችን ችግር ላይ ባለበትና ከስር ጀምሮ በቂ ውይይት ባልተደረገበት ሁኔታ ይህ ስብሰባ መጠራት የለበትም የሚል አቋም በመያዛቸው በሻይ ዕረፍት ስም ስብሰባው ከአንድ ሰዓት በላይ ተቋርጦ ለማግባባት ቢሞከርም ሳይሳካ ቀርቷል።
በስብሰባው ላይ የተገኙትና የመጀመሪያውን የተቃውሞ ደምጵ ያሰሙት የኦሮምያ ኮምኒኬሽን ጵ/ ቤት ሀላፊ አቶ አዲሱ አረጋ ባደረጉት ንግግር ከ600 ሺህ በላይ ህዝባችን በኦሮምያና ሶማሌ ግጭት በተፈናቀለበትና በየቦታው ግጭቶች በቀጠሉበት፣ ረቂቅ አዋጁም ህዝባችን ባልተወያየበት ሁኔታ ይህ ስብሰባ መጠራት እንደሌለበት በመጥቀስ ለሌላ ግዜ እንዲተላለፍ ጠይቀዋል። ይህን የአቶ አዲሱ ንግግር አብዛኛው የኦህዴድ የፓርላማ አባላት በጭብጨባ ድጋፍ ሰጥተዋል።
ከኢህአዴግ ስብሰባ አቋርጠው በድንገት የተገኙት አቶ አባዱላ ገመዳ ከአብዛኛው የኦህዴድ አባላት በተቃራኒ ስብሰባው እንዲቀጥል ሀሳብ ሰጥተዋል። ረቂቅ አዋጁ የቀረበው ለማዳበር እንጅ ለማጵደቅ አለመሆኑን፣ ሌሎች መድረኮች ወደፊት እንደሚኖሩና መወያየቱ ጥቅም እንጅ ጉዳት እንደሌለው ያደረጉት ገለጳ የአባላቱን የጉምጉምታ ተቃውሞ አስከትሎአል።
እንደአቶ አባዱላ ስብሰባ አቋርጠው የተገኙት አቶ አስመላሽ ወልደስላሴ ባቀረቡት ሀሳብ መሰረት ስብሰባው ለሻይ ዕረፍት ተበትኖ ከአንድ ሰአት በላይ ቆይቷል። በዝህ ሰዓት የኦህዴድ የፓርላማ አባላት አቶ አባዱላ ባሉበት በኦሮምኛ ቋንቋ የማግባቢያ ስብሰባ የተደረገ ቢሆንም አባላቱን ሀሳባቸውን ማስቀየር አልተቻለም።
በአካሄድ ውዝግብ እስከጠዋቱ 5:30 ሰአት በመቀጠሉ ጊዜም ስለሌለ በሚል የቋሚ ኮምቴው ሰብሳቢ ወደሌላ ቀን እንዲዛወር ያቀረቡት ሀሳብ ተቀባይነት በማግኘቱ ስብሰባው ተበትኗል

No comments:

Post a Comment