Friday, August 18, 2017

በወልድያ ተቃውሞ መቀስቀሱ ተሰማn source mereja

በወልድያ ተቃውሞ መቀስቀሱ ተሰማ
በወልድያ ተቃውሞ መቀስቀሱን ምንጮች ጠቆሙ፡፡ በዛሬው ዕለት የወልድያ ህዝብ ‹‹አላግባብ የተጫነብኝን ግብር አልከፍልም፡፡›› ብሎ አሻፈረኝ ማለቱን ከስፍራው የተገኘው መረጃ አመልክቷል፡፡ በዚህም የተነሳ ከተማው ውጥረት ማርገዙን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ባለፈው ሳምንት ለአምስት ቀናት የስራ ማቆም አድማ ላይ የሰነበተው የወልድያ ህዝብ፣ በዛሬው ዕለትም ተቃውሞ አስነስቷል፡፡ የህወሓት መንግስት በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ ነጋዴዎች ላይ ከፍተኛ የግብር ጫና መጣሉ አይዘነጋም፡
በሀገሪቱ ነጋዴዎች ላይ የተጫነውን የግብር ጫና ተከትሎ በመላው ሀገሪቱ ተቃውሞ መቀስቀሱ የሚታወስ ሲሆን፣ ወልድያም ተቃውሞ ከተቀሰቀሰባቸው ከተሞች አንዷ ሆና ሰንብታለች፡፡ በዛሬው ዕለት ተቃውሞው በድጋሚ ማገርሸቱን የተናገሩት የከተማዋ የቢቢኤን ምንጮች፣ ህዝቡ ግብሩ ካልተቀነሰለት በቀር ለመክፈል ዝግጁ አይደለም ብለዋል፡፡ ምንጮቹ አክለውም ‹‹በግብር ስም ዘረፋ መፈጸም ተገቢ አይደለም፡፡›› ሲሉም የህወሓትን መንግስት የዘረፋ አዝማሚያ ተችተዋል፡፡
የከተማዋ ህዝብ ግብር አልከፍልም ማለቱን ተከትሎ፣ የፖሊስ ኃይሎች በከተማዋ መሰማራታቸውን የገለጹት ምንጮች፣ እስከ ምሽቱ አንድ ሰዓት ድረስም ከተማዋ ውጥረት ላይ እንደነበረች ይገልጻሉ፡፡ ከምሽቱ አንድ ሰዓት በኋላ ከተማዋ ጭር ብላ መታየቷን የገለጹት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ መሸት ካለ በኋላ የፖሊሶች ቁጥር ጨምሮ መመልከታቸውን ተናግረዋል፡፡
ጥያቄአቸው እስካልተመለሰ ድረስ፣ የዛሬው ተቃውሞ በነገው ዕለትም ሊቀጥል እንደሚችል ነዋሪዎቹ አረጋግጠዋል፡፡ በኦሮሚያ ክልል ከግብር ጫና ጋር በተያያዘ ተቃውሞ ከተነሳ በኋላ፣ መንግስት የግብር ቅነሳ ይደረጋል የሚል ማስተባበያ ቢሰጥም፣ በመጨረሻም ግን ውሸት መሆኑ ተረጋግጧል፡፡
BBN

Monday, August 14, 2017

ኢትዮጲያ የማን ናት? መብቱ የዜጎች፣ ስልጣኑ የብሔሮች ነው – ክፍል 2 – ስዩም ተሾመ source zehabesha

“ኢትዮጲያ የማን ናት፡ የብሔሮች ወይስ የዜጎች?” በሚል ርዕስ ባወጣነው የመጀመሪያ ክፍል የኢህአዴግ መንግስት ባለፉት አስር አመታት ፍፁም አምባገነን እየሆነ መምጣቱን ተመልክተናል። ለዚህ ደግሞ ዋና ምክንያቱ ከሕገ-መንግስቱ መሰረታዊ መርሆች ውስጥ “የሕዝብ ሉዓላዊነት” በሚለው መርህ ላይ መንጠልጠሉና በዚህም ራሱ የዘረጋውን ሕገ-መንግስታዊ ስርዓት ቀልብሶታል።
በመሰረቱ፣ “የሕዝብ ሉዓላዊነት” የሚለው ሕገ-መንግስታዊ መርህ ከሀገርና መንግስት አመሰራረት ፅንሰ-ሃሳብ ጋር ይጋጫል። ሌላው ቀርቶ ከሕገ-መንግስቱ ጋር ራሱ ይጋጫል። በአጠቃላይ “የሕዝብ ሉዓላዊነት” የሚለው መርህ “ፀረ-ዴሞክራሲያዊ” ነው። “በእንቅርት ላይ ጆሮ-ደግፍ” እንዲሉ መንግስታዊ ስርዓቱ ደግሞ በዚህ መርህ ላይ እንደመሆኑ ሕገ-መንግስቱ፥ ብሎም ፖለቲካዊ ስርዓት ካልተቀየረ በስተቀር ዴሞክራሲ “ላም አለኝ በሰማይ…” እንደሚሉት ሆኖ ይቀራል። በዚህ ፅሁፍ፣ “ከሕዝብ ሉዓላዊነት” መርህ አንፃር የኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት እርስ-በእርሱ እንደሚጋጭ እንመለከታለን። በቀጣይ ክፍል ደግሞ ከሀገርና መንግስት አመሰራረት አንፃር የተሳሳተ መሆኑን እንመለከታለን።
ስዩም ተሾመ
በኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 8 መሰረት “የኢትዮጲያ ብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች የኢትዮጲያ ሉዓላዊ ስልጣን ባለቤቶች ናቸው”።ነገር ግን፣ ይህ መርህ ከሉዓላዊነት ፅንሰ-ሃሳብ ጋር ይጋጫል። በዚህ ረገድ ያለውን የተሳሳተ እሳቤ በግልፅ ለመረዳት እንዲያስችለን የሕገ-መንግስቱን የቃላት አጠቃቀም እና የኢትዮጲያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል በ1993 ዓ.ም ያዘጋጀውን የኣማርኛ መዝገበ ቃላት መሰረት በማድረግ ፅንሰ-ሃሳቡን በዝርዝር እንመለከታለን።
በኢፊዲሪ ሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 39(5) መሰረት “ብሔር፥ ብሔረሰብ፥ ሕዝብ” ማለት ሰፋ ያለ የጋራ ባህሪይ የሚያንፀባርቅ ባህል ወይም ተመሳሳይ ልማዶች ያሉት፣ ሊግባባበት የሚችልበት የጋራ ቋንቋ ያለው፣ የጋራ ወይም የተዛመደ ሕልውና አለን ብለው የሚያምን፣ የሥነ ልቦና አንድነት ያለውና በአብዛኛው በተያያዘ መልክዓ ምድር የሚኖር “ማህብረሰብ” ነው። (የቃላት ድግግሞሽን ለማስቀረት ሲባል እንደየሁኔታው “ብሔር፥ ብሔረሰብ፥ ሕዝብ” የሚለው “ብሔር” ተብሎ ሊፃፍ ይችላል።) በዚህ መሰረት፣ ብሔር በቋንቋ፥ ባህል፥ ልማድና ስነልቦናዊ አመካከት፣ እንዲሁም በታሪክ፣ ኢኮኖሚና በመልክዓ ምድር የተሳሰረ ማህብረሰብ ነው። በመሆኑም፣ የብሔር መብቶች ከእነዚህ ተፈጥሯዊ ባህሪያት ጋር በቀጥታ የተያያዙ ናቸው። በኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 39 ላይ “የብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች መብት” በሚል የተጠቀሱት ዴሞክራሲያዊ መብቶች ይህን ያመለክታሉ።
መሰረታዊ መብቶችና ነፃነቶች በተደነገጉበት የሕገ-መንግስቱ ምዕራፍ ሦስት ክፍል ሁለት መሰረት፣ በንዑስ አንቀፅ 39(1) “ማንኛውም ብሔር የራሱን ዕድል በራሱ የመወሰን እስከመገንጠል መብት”፣ በንዑስ አንቀፅ 39(2) “ማንኛውም ብሔር በቋንቋው የመናገር፥ የመፃፍ፥ ቋንቋውን የማሳደግ እና ባህሉን የመግለፅ፥ የማዳበርና የማስፋፋት፣ እንዲሁም ታሪኩን የመንከባከብ መብት”፣ በንዑስ አንቀፅ 39(3) ደግሞ “ማንኛውም ብሔር ራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ መብት” እንዳለው ተገልጿል። ከዚህ በተጨማሪ፣ በሕገ-መንግስቱ ንዑስ አንቀፅ 40(3) መሰረት “የመሬት ባለቤትነት መብት”፣ እንዲሁም በንዑስ አንቀፅ 43(1) መሰረት ደግሞ “የልማት መብት” እንዳላቸው ይጠቅሳል።
በዋናነት በሕገ-መንግስቱ እውቅና የተሰጣቸው የብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች መብቶች ከላይ የተጠቀሱት ብቻ ናቸው። ከዚህ በተረፈ፣ በሕገ-መንግስቱ ምዕራፍ ሦስት ክፍል አንድ ስር የተዘረዘሩት በሙሉ የግለሰብ ሰብዓዊ መብቶች ናቸው። በክፍል ሁለት ከተዘረዘሩት ውስጥ ከአንቀፅ 39፣ ንዑስ አንቀፅ 40(3) እና 43(3) በስተቀር ያሉት በሙሉ የግለሰብ ዴሞክራሲያዊ መብቶች ናቸው። ከዚህ በተጨማሪ፣ እያንዳንዱ ግለሰብ ግን እንደ አንድ ብሔር ተወላጅ ከላይ የተጠቀሱት የብሔር መብቶች ይኖሩታል።
የአማርኛ መዝገበ ቃላት “ሉኣላዊ” (Sovereign) የሚለውን ቃል “ነፃ የሆነ መሬት፣ ነፃ የሆነ፥ ምሉዕ ስልጣን ያለው ሀገር፥ መንግስት” የሚል ፍቺ ይሰጠዋል። “ሉዓላዊነት” (Sovereignity) ማለት ደግሞ “ምሉዕ የሆነ መብት፥ የነፃነትና ሥልጣን የበላይነት” እንደሆነ ይገልፃል። በዚህ መሰረት፣ “የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት” የሆነ አካል በቅድሚያ ምሉዕ መብትና ነፃነት ሊኖረው ይገባል።
በአጠቃላይ፣ በሕገ-መንግስቱ የተደነገጉት ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በሙሉ መሰረታዊ የግለሰብ መብትና ነፃነት ሊሆኑ ይችላሉ። የብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች መብቶች ግን በአንቀፅ 39፣ 40(3) እና 43(3) የተጠቀሱት መብቶች ብቻ ናቸው። በዚህ መሰረት፣ አንድ ግለሰብ ምሉዕ መብትና ነፃነት አለው። በተቃራኒው አንድ ብሔር፥ ብሔረሰብ ወይም ሕዝብ ግን ምሉዕ መብትና ነፃነት የለውም።
ቀደም ሲል ለመግለፅ እንተሞከረው፣ “ሉኣላዊነት” (Sovereignity) ማለት “ምሉዕ የሆነ መብት፥ የነፃነትና ሥልጣን የበላይነት” ነው። በዚህ መሰረት፣ አንድ ብሔር፥ ብሔረሰብ ወይም ሕዝብ ሉዓላዊ ስልጣን እንዲኖረው በቅድሚያ ምሉዕ መብትና ነፃነት ሊኖረው ይገባል። ነገር ግን፣ በሕገ-መንግስቱ ምዕራፍ ሦስት ክፍለ አንድና ሁለት ስር ከተዘረዘሩት 31 መሰረታዊ መብቶችና ነፃነቶች ውስጥ የብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች መብት የሆኑት በአንቀፅ 39፣ ንዑስ አንቀፅ 40(3) እና 43(3) የተጠቀሱት ብቻ ናቸው። ከእነዚህ ውጪ ያሉት በሙሉ የግለሰብ መብቶች ናቸው።
እያንዳንዱ ግለሰብ በአንቀፅ 39፣ ንዑስ አንቀፅ 40(3) እና 43(3) የተጠቀሱት የብሔር መብቶች እንደ አንድ ብሔር ተወላጅ ይኖሩታል። እያንዳንዱ ብሔር ግን በአንቀፅ 39፣ ንዑስ አንቀፅ 40(3) እና 43(3) ከተጠቀሱት ውጪ ሌላ ዴሞክራሲያዊ መብት ሊኖረው አይችልም። ምክንያቱም፣ ብሔር፥ ብሔረሰብ፥ ሕዝብ እንደ ግለሰብ በራሱ ሃሳብና አመለካከት የሚንቀሳቀስ ምክንያታዊ ፍጡር ስላልሆነ ሌሎች ዴሞክራሲያዊ መብቶች የሉትም። በተመሳሳይ፣ እንደ ሰው ሰብዓዊ ፍጡር ስላልሆነ “ሰብዓዊ” መብት ሊኖረው አይችልም። ስለዚህ፣ በሕገ-መንግስቱ ራሱ ምሉዕ መብት ያለው ግለሰብ እንጂ ብሔር፥ ብሔረሰብ ወይም ሕዝብ አይደለም።
በአጠቃላይ፣ የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት መሆን የሚችለው እያንዳንዱ ኢትዮጲያዊ ዜጋ እንጂ የኢትዮጲያ ብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች አይደሉም። ምክንያቱም፣ የኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት በምዕራፍ ሦስት ስር ከዘረዘራቸው 31 መሰረታዊ መብቶች ውስጥ ሦስት መብቶች ብቻ ያሏቸው ብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች “የኢትዮጲያ ሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት” እንደሆኑ ይገልፃል። ነገር ግን፣ “ሉኣላዊነት” የምሉዕ መብትና ነፃነት ባለቤትነት እንደመሆኑ መጠን ውስን መብት ያላቸው ብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤትነት ሊኖራቸው አይችልም። በዚህ መሰረት፣ የኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት እርስ-በእርሱ እንደሚጋጭ በግልፅ መረዳት ይቻላል።
በመጨረሻም፣ በሕገ-መንግስቱ መሰረት እያንዳንዱ ኢትዮጲያዊ ዜጋ ምሉዕ የሆነ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብት አለው። በዚህ መሰረት፣ የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት መሆን የሚችሉት ሁሉም ኢትዮጲያዊያን ወይም ሁሉም የሀገሪቱ ዜጎች ናቸው። ይሁን እንጂ፣ በሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 8 መሰረት “የኢትዮጲያ ብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች የኢትዮጲያ ሉዓላዊ ስልጣን ባለቤቶች እንደሆኑ ተደንግጓል። ስለዚህ፣ ሕገ-መንግስቱ እርስ-በእርስ እንዲጋጭ የተደረገበት ምክንያት ምንድነው?
በመሰረቱ፣ የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት የሆነ አካል ባለመብት ብቻ ሳይሆን ባለስልጣን ጭምር ነው። ምክንያቱም፣ ሉዓላዊ ስልጣን ያለው አካል በሀገሪቱ መንግስት ላይ የስልጣን የበላይነት ይኖረዋል። ስለዚህ፣ የሀገሪቱ መንግስት ተጠሪነቱ ለዚህ አካል ይሆናል። በኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት መሰረት፤ የሀገሪቱ ዜጎች መብትና ነፃነት አላቸው፣ ብሔሮች ደግሞ የሉዓላዊ ስልጣን አላቸው። ዜጎች ምሉዕ መብት አላቸው፣ ነገር ግን መብታቸውን የመጠየቅ ምሉዕ (ሉዓላዊ) ስልጣን የላቸውም። ብሔሮች ደግሞ ምሉዕ (ሉዓላዊ) ስልጣን አላቸው፣ የሚጠይቁት ምሉዕ መብት ግን የላቸውም። በኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት መሰረት መብቱ የዜጎች ሲሆን ስልጣኑ ግን የብሔሮች ነው!
በአጠቃላይ፣ የሀገሪቱ ዜጎች የማይጠይቁት መብት ሲኖራቸው፣ የሀገሪቱ ብሔሮች ደግሞ የማይጠቀሙት ስልጣን አላቸው። የኢህአዴግ መንግስት ዘወትር ስለ ብሔር መብትና እኩልነት ይደሰኩራል። ዜጎች የመብትና እኩልነት ጥያቄ ሲያነሱ ግን እንደ ጠላት እያደነ ያስራል፥ ይገድላል፥…ወዘተ።

Friday, August 11, 2017

የሜቴክ ውንብድና….በአዲስ አበባ ትራንሰፖር አውቶቢስ ግዢ ላይ (ጥብቅ መረጃ) source zehabesha

በበዛብህ ሲሳይ (2009) ሀይድራባድ ህንድ
ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ ሰሞኑ በቀድሞ የስርዓቱ ልሳን በነበረው በአቶ ኤርሚያስ ለገሰ ሜቴክ ከንግድ መርከብ ስለገዛቸው ሁለት መርከቦችና ሊያቋቁመው ስላሰበው የውሃ ትራንስፖርት ንግድ ስራ እንዲሁም በአገሪቷ ላይ ያደረሰውን ኪሳራ ካይሁ በኃላ ነው፡፡ እውነት ነው ተቋሙ ሲቋቋም ጀምሮ ለገዢው ጉጅሌ ኢኮኖሚያዊ ትርፍ እንዲያመጣ ተብሎ ብቻ አይደለም የትግራይ ተወላጆችን ከሰሜን ኤርትራዋኖች ላይ እንዲሁም ከደቡብ ደግሞ ሰፊው የኢትዮጰያ ህዝብ ላይ የፖለቲካዊ ልእልና እንዲያመጣ ጭምር እንጂ፡፡ ስለዚህ አቶ ኤርምያስ እንደ አስቀመጠው የሜቴክ መሪዎቹ ሲጋራን በቄንጥ ሚያጨሱ ብቻ ሳይሆኑ በዚህ እኩይ አላማቸው ላይ የሚሳተፉትን ሆድ አደር “ሙሁራን” ወይም ባለሰርተፊኬቶችን ወይም እንዴት ማስተዳደርና መጠቀም እንዳለባቸው ስለሚያውቁ ይሄው ይሄ ሁሉ ጉዳት በአገሪቱ ላይ ሊያደርሱ ቻሉ፡፡ አንዳንዴ የፈረንጅንም ጫማ ላሾችንም (Bootlikers) ይጠቀማሉ፡፡ በዚህ ጽሁፍ ዋና አላማ ሜቴክ ተልዕኮውን እንዴት እንደሚያሳካ ለማሳይት የታሰበ ሲሆን ፅህፉ ያለውን ነባራዊ ሁኔታን ብቻ የሚያሳይ ነው..ፍርዱን ደግሞ እናነተ ስጡ… መልካም ንባብ !!

በመጀመሪያ ግን አንባቢያን ሊገነዘቡት የምፈልገው ሜቴክ መቆጣጠር ሚፈልገው የኢኮኖሚ አውታር በዋነኝነት ከአገር ውስጥ ወይም ከዉጭ ሃገር ልዪ የፋይናንስ ድጋፍ ያላቸውን ፕሮጀክቶች ሲሆን ትራንስፖርት ደግሞ ዋነኛ ነው ምክንያቱም ከአለም ባንክ ወይም ከቻይና ኤግዚም ባንክ አብዛኛው ብድር የሚሰጠው ለመሰረተ ልማት ግንባታ በመሆኑ ነው፡፡ ሜቴክ ገና ጥርሱን ሳይነቅል ዘሎ ዝርፊያውን የጀመረው የቀድሞ ኢትዮ- ጂቡቲ ባቡር ሃዲድ ላይ ጉብ በማለት ነው፡፡ ለተበተነው የባቡር ሰራተኞች ደሞዝ እከፍላለሁ በሚል ተልካሻ ሰበብ በ1907 የተመረተውን ንፁህ የባቡር ሃዲድ ብረት ወረሰው፡፡ ካለምንም ማስረጃ፡፡ ለዚያውም በ ፈረንጆች 2006 ከአውሮጳ ህብረት በተገኘ የ50 ሚሊዮን ዩሮ ብድር የመልሶ ማቋቋም እድሳት ስራ ጀምሮ የነበረውን እንዲቋረጥ በማድረግ ነው (ግርጌ ፎቶውን ይመልከቱ)፡፡ በመስኩ የተሰማሩት ባለሞያዎች እንሚሉት የቀድሞ የባቡር መስመር በትክክል ቢሰራ ኢትዮጵያ የምታስገባውንም ሆነ የምታስወጣውን ጭነት በአስተማማኝ ከማስተናገዱ አልፎ ሃገሪቱ በሚቀጥሉት ሃያ አመታት ልታመጣው የምትችለውን የኢኮኖሚ እድገትም መሸከም የሚችል ነበር፡፡ ይሄ ለነክንፈ እና አርከበ አይገባቸውም፡፡ የአዲስ አበባ ባቡርም በሰዓት ሃያ ሺህ ህዝብ ያመላልሳል በለው ጉፋያአቸወን ነፍተው አመት እንኳን ሳያገለግሉ ግማሽ ያህሉ ወላለቀው መሃል ሜዳ ላይ ቆሙ!! ሌላው ቢቀር ኢትዮ- ጂቡቲ ባቡር ታሪካዊነቱ ታይቶ ልክ በሰለጠኑት አገራት እንደሚገኙት የድሮ የባቡር መስመሮች ለቱሪዚም አገልግሎት መዋል ይችል ነበር፡፡ በተለይ ከአዲሱ መስመር በበለጠ በብዙ ከተሞች ላይ ማረፊያ ተሪሚናሉች ስላሉት ከተሞችን በንግድ በማስተሳሰር ከፍተኛ አስተዎጽኦ ማምጣት ይችል ነበር፡፡ይሄም ባቡር ወደ 32 ሚሆን ቦታ ላይ ሲያርፍ የቀድሞ ግን ከ100 በላይ ቦታዎች ላይ በማረፍ የከተሞች የኢኮኖሚ እና የማህበረሰብ ትስስርን ያጠናክር ነበር፡፡ ሆኖም ለታሪክ ደንታ የማየሰጣቸው የትግራይ ጉድሌዎችን ያቀፈው ሜቴክ ታሪካዊዉን የበቡር ሃዲድ ብረት ሃላፊነት በጎደለው መንገድ ስልቅጥ አድርጎ በላው፡፡

ከዚህ የረቀቀ አገርን የማውደም ሴራ በሰተጀርባ ያለውን ለመረዳት ግን ከጀነራሎቹ ጋር በመሆን ለሜቴክ ጭንቅላት የሆኑትን ሆድ አደር ምሁራን ተብየዎችንም አብረን ማየት ያለብን፡፡ ምክንያቱም ጠቋሚዎቹና አስተባባሪዎቹ እነሱ ስለሆኑ!!!
ሙሁር ተብየዎችን በማፍራት ግንባር ቀደም የሆነው ገና ከተቋቋመ 20 አመት በሞላው የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን የሜቴክን አላማ የሚተገብሩለትን በላተኞችን የሚኮተኩትበት ዋነኛ ወታደራው ተቋም ነው፡፡ አካዳሚያዊነቱን ግን ብላሽ ብቻ አይገልፀውም፡፡ አንዴ እዚያ የሚያስተምር ጓደኛየን C ሰጠኅን ብለው ደብድበውታል፡፡ ከዚህ ተቋም የሚመረቁ “ባለሞያዎች” የወታደር ስነ-አምሮ የተላበሱ በመሆናቸው በሲቨል ተቋም ዉስጥ ሲገቡ ይሄንን የመታዘዝና-የማዘዝ ህግጋትን ስለሚተገብሩ ወይም በውይይትና የአመክንዮ ልእልና ስለማያምኑ በሜቴክ አለቆች ዘንድ እጅጉን ጀርባ የሚጣልባቸውና የሚወደዱ ናቸው፡፡ በዩንቨርሲቲው ትምህርት ላይ እያሉም እርስ-በራስ የመገማገምን ትምህርትና የሰዎችን ጉልበት ማሟጠጥ የሚችሉበትን ክህሎት ይቀስማሉ፡፡ ስለዚህ ወደ ስራ ሲገቡ የራሳቸውን ኔትዎርክ በቶሎ ይዘረጉና ምዝበራውን ያሯሩጡታል፡፡ በለራዕዩ መለስ አገሪቱ የተማረ ወታደር አያሰፈልግጋትም ካለ ከዚህ ተቋም የሚወጡት ለሌላ አላማ ነው ማለት ነው፡፡
ከዚህ ቀጥሎማ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ተቋማቶችን በአይን በመማተር ለአለቆቻቸው ሹክ ይላሉ፡፡ ገሚሱን ቻይና በመላክ የውንብድና ሊቅ ሲያረጉዋቸው የተቀሩትን ደግሞ አይናቸውን ጨፍነው አገራዊ (local) ሮል ሞዴል እንዲያበጁ ያረጓቸዋል፡፡ እኔም ከአምስት ከማያንሱ የቀድሞ የስራ ባለደረቦቼ የተረዳሁት አብዛኛዎቹ መለስን እንዲሁም ጥቂቶቹ ስየን እንደ ትልቅ ሮልሞዴል እንደሚዩዋቸው ነው፡፡ ሁለት ዘራፊዎችን!!! ከዚህ ዝግጅት በኃላ ወደ ሲቭል ተቋማት በማስገባት ነባር ተቋማትን በማፍረስ በምትካቸው አዳዲስ ለሚቋቋሙጽ ስም በመስጠት በሮዎችን መክፈት !…ለምሳሌ ኤጀንሲ ፣ባለስልጣን፣ ፅ/ቤት ፣ ተቆጣጣሪ፣ …የረሳሁት ካለ አግዙኝ! ከዚህም አዳዲስ የሚቋቋሙበት ዋና አላማ ተቋሙን ለማደራጀት ተብሎ ከሚመደበው የማቋቋሚያ ገንዘብ ለቤት ክራይ፣ ለጠረቤዛ፣ ለመኪና፣ ..ወዘተ ብለው እንዲጨርሱትና አዳዲስ ተቋማት ውስጥ የራሳቸውን ሰዎች በመሰግሰግ ወደፊት ለሚዘርፉት መንገድ በማበጀት ተጠያቂነት ፈፅሞ እንዳይኖር ለማድረግ ነው፡፡
የሜቴክ መሰሪ አላማ ለመመልከት እስቲ የአዲስ አበባ የመንገዶችና ትራንስፖርት ቢሮን እንይ፡፡ በ2005 ከንቲባ ደሪባ ኩማ ሲሾሙ የከተማይቱን የትራንሰፖርት ችግር ይቀርፋሉ ተብሎ በሰፊው ተዘግቦ ነበር፡፡ በተለይ ፎርቹንና ሪፖርተር ከተቋሙ ጋር ልዩ ጥቅም ስላላቸው የማይመስል ወሬ በማራገብ አንደኛ ናቸው-ለምሳሌ አዲስ አበባ የብስኪሌት ታክሲ ልታገኝ ነው (1 ቀን ሳየሰራ 16 ሚሊዮን ብር አፈር ድሜ ያበላና የከተማዋ ነዋሪዎችም ሽንታቸው እስኪለቁ የሳቁበት)…..15 ፎቅ ያለው ዘመናዊ በኤሌክትሪክ የሚሰራ ፓሪኪንግ ተመረቀ (አጠገቡ ያሉ ኢንተርኔት ቤቶች በኤሌክትሪክ መጥፋት ስራቸውን እንደተዉ ከንቲባው ሳይሰማ ለአድቬንቸር ብሉ የ85ሚሊዮን የብረት ሼልፍ ይመርቃል)… ሌላም ብዙ ብዙ፡፡
ወደ ትራንስፖርት ቢሮው ልመለስና የከተማው ነዋሪ ያለበትን የትራንሰፖርት ችግር ለመቅረፍ አዲስ ተቋም ያስፈልጋል በሚል የትራንስፖርት ፕሮግራሞች ማስተባበሪያ ፅ/ቤት በሚል እንዲቋቋም ይደረጋል፡፡ ይታያቹህ ለዝርፊያው ያመች ዘንድ መጀመሪያ የፕሮጀክት ማስተባበሪያ ተብሎ የነበረው ፅ/ ቤት ባንዴ እንጣጥ ብሎ የፕሮግራም ማሰተባበሪያ ሆነ! እውነቱ ግን በየትኛውም አለም የተለያዩ ፕሮግራሞችን ማሰተባበር አይቻልም … የእውር መንገድ ለመሆኑና ለመዝረፍ ተብሎ በሜቴክና በከንቲባው የተቀናበረ እንደሆነ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ እንደ ፀጉራም ዉሻ አግዝፈው ትልቅ በጀት ለመመደብ እንደሆነ ለሁሉም ባለሞያ ግልፅ ነበር፡፡ የሆነውም ይህንን ተቋም እንዲመራ በብ/ጀ ክንፈ ዳኜው የተመደበው የመከላከያ ዩንቨርሲቲ ምሩቁና የቀድሞ የመረጃ ደህንነት ሰራተኛ የነበረው ዶ/ር ሰለሞን ኪዳኔ ሲሆን ከመጀመሪያውኑ የሜቴክን አላማ ለማሳካት የተተከለ ወታደር ነው፡፡

በመጀመሪያ አዲስ የሚቋቋሙትን ተቋማት ከመደበኛ የሲቪል ሰርቪስና የፋይናንስ ቢሮክራሲ በማስወጣት በቦርድ እንዲተዳደር ማድረግ ሲሆን የቦርድ አባላቱም ባብዛኛወቹ አብሮ በላተኞችና በዶ/ሩ የተመረጡና የቀድሞ የመከላከያ ምሩቃንን የሚያጠቃልል ነበር፡፡ ከንቲባውም ቦርዱን አንድ ቀን ሳይሰበስበው ዶ/ሩ ሁሉን የሚያዝ ሆነ፡፡ ከዚህ በኃላማ ማን ይመልሰው……ልጁ ቀማኛ …አባቱ ዳኛ ሆነው እርፍ! የከተማይቱ ነዋሪ የሚፈልገው ግማሽ ኪሎሜትር ከሚደርሰውን የታክሲ ወረፋ የሚገላግለው ሆኞ ሳለ ባለ 15 ፎቅ ፓርኪንግ፣ ደብል ዴክ የአቶቢስ ማቆሚያ፣ ተርሚናሎች፣ የማይሰሩ የትራፊክ መብራቶች በየአደባባይ መትከል….ብቻ በአጠቃላይ ሜቴክ እንደሚያረገው ጉፋያውን መንፋት ብቻ ሆነ፡፡ ለዚህም ከከንቲባውና ምክትሉ አቶ አባተ ስጦታው ጋር ልዩ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ነባሩን አንበሳ አውቶቢስን (ከአፄው ጊዜ ጀምሮ የነበረ) እንደማጠናከር ፋንታ ሌላ በዚሁ ትራንስፖርት ቢሮ ስር የሚተዳደር አዲስ ሸገር አውቶቢስ የሚባል በመፍጠርና ሜቴክን በአውቶቢስ ግዢ ማክበር ሆነ ዋነኛው አላማ፡፡ በአምባሳደር ሱለማን ደደፎ ደብዳቤ ላይ እንደተገለፀው አዲስ የመርከብ ንግድ ሊጀምሩ እንዳሰቡት ማለት ነው!
ለዚህም ከመስተዳድሩ የሚበጀትና ከአለም ባንክ ሊገኝ ከታሰበው ከ300 ሚሊዮን ዶላር አብዛኛው ለሜቴክ አውቶቢስ መግዢያና ለትራፊክ መብራት መትከያ የሚውል ሲሆን ሜቴክ እስከ አሁን ወደ 1000 አውቶቢስ አገር ዉስጥ ገጣጥሞ ለመስተዳድሩ ያስረከበ ሲሆን አሁን ደግሞ የ750 አውቶቢስ አዲስ ውል አስሯል፡፡ እንደ ሪፖርተር ጋዜጣ ሃተታ ሜቴክ አንዱን አውቶቢስ በ3.6 ሚሊየን ብር ሲሸጥ ሌላው በግል የሚተዳደረው አልያንስ ባስ ደግሞ ተመሳሳይ አውቶቢስ በ 1.6 ሚሊየን ከቻይና ያለቀለት ያስመጣል፡፡ ልዩነቱ የአልያንስ አውቶቢስ ካሜራ ስላልተገጠመለት ብቻ ነው!! በጣም አስቂኝና የሜቴክ- ከንቲባው ድብቅ አላማ ፍንትው አድርጎ ያሳያል፡፡ ይሄም ሜቴክ አደናጋሪ ቃላት በሲቨል መስሪያቤቶች በወተፋቸው ወታደሮቹ እያስነገረ ህዝቡን ማደኸየትና መሰረታዊ ለውጥ በማሓከለኛው ሃገር እንዳይመጣ በማድረግ የፖለቲካዊ አላማውን ያስፈፅማል፡፡ ሌላው የሜቴክ ዘመዶች ደግሞ የተሳተፉበት የሰብ-ኮንትራት ቢዝነስ በትራፊክ መብራት በመትከል ሰበብ ዘመዶቻቸውን ዊስኪ ጨብጠው ለሊቱን እንዲያነጉ ያደረጓቸዋል፡፡ ለዚህም ወደ 170 ሚሊየን ዶላር አዲስ የተመደበ የወንበዴው ወርልድ ባንክ ብድር መንገድ ላይ ነው፡፡ ለዚሁም የጠቅላይ ሚኒስትሩ ወንድም አቶ ገነቱ ደሳለኝን ስራ አስኪያጅ አድርጎ ዝርፊያውን መሸፋፈንና አጋላጭ እንዳይኖር ማድረግ ነው፡፡
ይህን ሁሉ ስናይ እነዚህ ሰዎች ሁዋላ ከማን ጋር ሊኖሩ ነው የሚለው የሚያስጨንቅ ጥያቄ በአምሮየ ይመላለሳል …..ውይይይ… ሰው ልቦና ከሌለው ለምንም አይሆንም…ለልጆቻቸው ግን ወየዎላቸው……..ግፉ ሲበዛ በሃይለኛው መልሶ ይገፋችኃል፡፡ በ 1960ዎቹ የተማሪ ንቅናቄ ጊዜ የምንለው ነበር……ነቅናቂው ተነቃናቂውን ሲነቀንቀው ተነቃናቂው ነቅናቂውን መልሶ ነቀነቀው!! …..ሰው እያወቀ ነው ዝም ያለው……. ልብ ግዙ ነው ምክሬ!!!! በሚቀጥለው ደግሞ ከዚሁ ጋር በተያያዘ በኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ኤጀንሲን ላይ አስነብባቹሃለሁ፡፡
ሠላም ሁኑ!

Wednesday, August 9, 2017

“የባህር ዳሩ ዕልቂት አይረሳም.. ሕዝቡ ሰማዕታቱን ሲያስብ አደራቸውን መርሳት የለበትም” – አክቲቭስት ሙሉነህ ዮሐንስ (ጠቃሚ መረጃዎችን የያዘ ቃለምልልስ) sorce zehabesha

“…በባህር ዳር በአንድ ቀን የፈሰሰው የንጹሃን ደም የሚረሳ አይደለም:: ሕዝቡ ሰማዕታቱን ሲያስብ አደራቸውን መርሳት የለበትም…የለውጥ ፈላጊው ተቃዋሚ እርምጃን በተለይ የእውነተኛ ትብብር አለመኖር አንዱ ከአንዱ ጋር ተባብሮ ያለመስራቱን በተመለከተ በተለይ ሚዲያው ግልጽ ውይይት የሚደረግበትን የህዝቡ ትግል በእውነት የሚደገፍበትን ለለውጡ የሚደረገው እንቅስቃሴ ትርጉም ያለው እንዲሆን ሀላፊነት ያለባችሁ ይመስለኛል…”  አክቲቪስት ሙሉነህ ዮሐንስ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከሰጠን ማብራሪያ (ቀሪውን ያድምጡት)






Tuesday, August 8, 2017

የብአዴን ነገር ( ግዛው ለገሰ ) source zehabesha

የብአዴን መስራቾች አንድማን እንደሆኑ ለሚያውቅ ሰው ብአዴን የአማራ ብሄርተኛ ድርጅት አለመሆኑን ለማወቅ ቀላል ነው:: የዘር ስብጥሩን  ስሌት ትተን የትግል መስመራቸውን ስናይ ቢያንስ ቢያንስ ኢትዮጵያ የብሔሮች እስር ቤት ናት የሚለው የዋለልኝ መኮንን የሞቅ ሞቅ ደቀመዛሙርት  መሆናቸውን እናያለን።
ስለሆነም የስልጣን ማንነታቸው ምሶሶ ለህወሓት ያላቸው ታማኝነት እንጂ የአማራ ብሄርተኝነት አይደለም:: የብሄርተኝነት መገለጫዎች የበላይነት ስነልቦና ፣ የታሪክ ማጋነን፣ የግዛት ማስፋፋት፣ የተጠቂነት  ትረካን ናቸው:: እነዚህ እሴቶች “እኛ” እና “እነሱ”፣ ወዳጅና ጠላት የሚለውን አጥር ይስራሉ:: ስለሆነም የ”አኛ” ቅርጫት ውስጥ ያለው በጭፍንነት የምታደርገውን ሁሉ ይደግፋል፣ ”እነሱ” ቅርጫት ውስጥ ያለውን በጠላትነት፣ በጥርጣሬ ይመለከታል። ይህ የህውሃት አርባ ዓመት አካሄድ ሲሆን አብዛኛው የግራይን ወጣት እና ምሁራን በከሏል::
ብአዴን በዚህ ሲለካ ባዶ ነው። መሪዎቹም፣ ተከታዮቹም፣ አብዛኛው ካድሬዎችም ብሄርተኞች አልነበሩም:: ግን ሰው በመሆናቸው ራሳቸውን መከላከል ተፈጥሯዊ ግዴታቸው ሊሆን ይገባ ነበር:: የዛሬ ዓመት በጎንደር እና በጎጃም የተነሳውን ሕዝባዊ አመጽ ተከትሎ የትግራይ ብሄርተኞች በብአዴን ላይ ከፍተኛ ቅስቀሳ በቀጣይነት እያኬያሄዱ ነው። አሁን አሁን የቅስቀሳው ስፋት እና ጥልቀት ህወሓት በማንፈስቶው ያስቀመጠው ታሪካዊ ተጠቂነት ትረካ ደረጃ ላይ የደረሰ ይመስላል። በመሆኑም ይወል ይደር እንጂ ህወሓት የገዛ ፍጡሩን ብአዴንን እንደገና ሊጠፈጥፈው መሆኑ ግልጽ ነው::
አመላካች ከሆኑት ክስተቶች አንዱ አሁን አሁን የአገሪቱ ችግሩ በሙሉ የብአዴን በ”ትምክህት” አስተሳሰብ መበከል ውጤት መሆኑ በህውሃት መዳፍ ስር በሚገኙት ሚድያዎች (EBC፣ ፋና፣ ዛሚ፣ ENN፣  Reporter፣ ሰንደቅ) እና በማህበራዊ ሚድያዎች እየተነገረ ነው።

ሙስና ብአዴን፣ መልካም አስተዳደር ብአዴን፣ የ”ጥልቅ ተሃድሶ” አዝጋሚነት ብአዴን፣ ሕዝባዊ አመጽ ብአዴን  ወዘተ  ሁሉም ነገር የብአዴን ችግር።
ሰሜን ጎንደር ውስጥ ስር እየሰደደ ያለው የመሳሪያ ታግል የብአዴን ቸልተኝነት፣ የወልቅይት ማንነት ጥያቄ የብአዴን ትምክህተኝነት፣ የኮሎኔል ደመቀ ጀግንነት የብአዴን አመራር ከጸረ ስርዓቱ ጋር ተባባሪነት ተደርገው እየተነገሩ ነው::
አሁን ደግሞ በጠራራ ጸሃይ በባህር ዳር በአልሞ ተኳሽ የተገደሉ ወጣቶች የብአዴን ሰለባዎች ተደርገው እየቀረቡ ነው። በህወሃት ብቻ ሳይሆን ተቃዋሚ ነን በሚሉ የትግራይ ተወላጆች  ለምሳሌ አስራት አብርሃም፣ አብርሃ ደስታ ወዘተ።
ይህ ሁሉ እየሆነ ለምንድነው ብአዴን ዝምታን የመረጠው? ድርጅቱ/መሪዎቹ ብይናገር/ሩ  አገር ቤትም ውጭም ያሉ ደገፊዎቹ ለምን መልስ አይሰጡም? የብአዴን ምሁራንስ ለምና ዝም አሉ? እውንስ ብአዴን ብሔርተኛ ቢሆን ይህን ሁሉ ጥቃት በዝምታ ያልፈዋል? ብአዴን ነጻ ድርጅት ቢሆን ኖሮ የሚደርደርበትን ወንጀል አይከላከልም?
የነዚህ ጥያቄዎች መልስ በብአዴን ውስጥ እውነተኛ ኢትዮጵያውያን እንደአሉ እውቅና ሰጥተን የሚቀጥለው ግንዛቤ መድረስ እንገደዳለን::
ብአዴን ብሔርተኛ አይደልም፣ ብአዴን የአማራ ድርጅት አይደለም፣ ብአዴን ነጻ አይደልም፣ ብአዴን ራዕይ የለውም። ብአዴን በህወሓት የተጸነሰ፣ በህወሓት የሚያስብ፣ በህወሓት የሚተኩስ፣ በህወሓት የሚወጣ፣ በህወሓት የሚወርድ የደካማ ግለሰቦች ይዞታ ነው:: ብአዴን አማራ ክልልን አይገዛም፣ ኦህዴድ ኦርምያን አይገዛም፣ ኢህአዴግ ኢትዮጵያን አይገዛም።
የሁሉም ገዢ ህወሓት ነው:: ህውሃት ሲሸነፍ፣ ብአዴን፣ ኦህዴድ ወዘተ ይሸነፋሉ:: ስለዚህ ሁሉም አይኖች ወደ ህወሓት!!

Monday, August 7, 2017

ባህርዳር የቤት ውስጥ የመቀመጥ አድማው በተሳካ ሁኔታ ተጀመረ | ንግድ ሱቆች ዝግ ናቸው | የከፈተ እርምጃ ይወሰድበታል እየተባለ ነው source zehabesha


(ዘ-ሐበሻ) የሕወሓት መንግስት የዛሬ ዓመት ነሐሴ 1 የገደላቸውን ከ50 በላይ ንጹሃን የባህርዳር ነዋሪዎችን ለማሰብ በዛሬው ዕለት የተጠራው ከቤት ያለመውጣት አድማ በዛሬው ዕለት በተሳካ ሁኔታ መጀመሩን የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታወቁ::
የዘ-ሐበሻ ምንጮች ከባህርዳር እንደገለጹት ሕዝብ ቤቱ ቁጭ ያለ ሲሆን ዛሬ በአድማ እንደሚውል ገልጸዋል:: ሱቆቻቸውን አንዳንዶች ከፍተው የነበረ ቢሆንም ማስጠንቀቂያ ሲደርሳቸው ወዲያው ዘግተው እንደሄዱም ከባህርዳር የመጣልን መረጃ ይጠቁማል::

Wednesday, August 2, 2017

ዶክተር መራራ ጉዲና ሁለት እጃቸውን ወደ ኋላ በካቴና ታስረው ፍርድ ቤት ቀረቡ source abbay media

ታዋቂው ፖለቲከኛና የፖለቲካ ሳይንስ መምህር ዶክተር መራራ ጉዲና ሁለት እጃቸውን ወደ ኋላ በካቴና ታስረው ፍርድ ቤት ቀረቡ።
በዘረፋ የታሰሩ እንዲሁም ነፍስ ያጠፉ ግለሰቦች ላይ የማይፈጸም ድርጊት ዶክተር መራራ ላይ መከሰቱ አነጋጋሪ ሆኗል።
ዶክተር መራራ ጉዲና ሁለት እጃቸውን ወደ ኋላ በካቴና ታስረው ፍርድ ቤት የማቅረቡ ርምጃ እሳቸውን በማዋረድ የደጋፊዎቻቸውን ቅስም ለመስበር ነው የሚለው የበርካቶች እምነት ነው። ርምጃው ደግሞ ቁጣን የሚቀሰቅስ መሆኑን የፖለቲካ ምሁራን ይናገራሉ።
በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ ሚና ይዘው የቆዩት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፕሬዝዳንት ዶክተር መራራ ጉዲና በአውሮፓ ሕብረት ግብዣ ቤልጂየም ብራስልስ መገኘታቸውን ተከትሎ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጥሰሃል በሚል መታሰራቸው ሲታወስ ቆይቶ ክሱ ወደ አሸባሪነት መለወጡ ይታወቃል።
ከሩብ ክፍለ ዘመን በላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያስተማሩትና ከዛሬ 40 አመት በፊት ጀምሮ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ትግል ውስጥ ተሳታፊና የለውጥና የመብት አቀንቃኝ የሆኑት ዶክተር መራራ ጉዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያለጊዜያቸው በጡረታ እንዲወጡ ያደረጋቸው ሲሆን አስፈላጊውን መመዘኛ አሟልተው የፕሮፌሰርነት ማእረግ እንደተነፈጉም ለኢሳት መግለጻቸው ይታወሳል።
ለረዥም ጊዜ ከኖሩበት ቤት መባረራቸውንም ተከትሎ አዲስ አበባ ጫፍ ላይ ተጀምሮ ወዳላለቀ ቤት መግባታቸውን ማስታውስ ተችሏል።
ዶክተር መራራ ጉዲና ሁለት እጃቸውን በካቴና ወደኋላ ታስረው ፍርድ ቤት የቀረቡት ዛሬ ማክሰኞ ሐምሌ 25/2009 እንደሆነም ታውቋል።
በነፍስ ማጥፋት፣በዘረፋ፣እንዲሁም በተራ ስርቆትም ሆነ በሌላ ወንጀል እንዲሁም በፖለቲካ ጭምር የታሰሩ በአብዛኛው በካቴና በማይታሰሩበት ሁኔታ እኚህን ታዋቂ ምሁርና ፖለቲከኛ በካቴና አስረው ፍርድ ቤት ያቀረቡበት ምክንያት አልታወቀም።