Thursday, July 13, 2017

የአገዛዙ ደኅንነቶች የኮሎኔል ደመቀን የ5 ዓመት ሕጻን ልጅ ለመጥለፍ ሙከራ አደረጉ source mereja.com

የአገዛዙ ደኅንነቶች የኮሎኔል ደመቀን የ5 ዓመት ሕጻን ልጅ ለመጥለፍ ሙከራ አደረጉ፤
 በኮሎኔሉ ላይ 9 የሰለጠኑ ምስክሮች ቃላቸውን ሰጥተዋል Muluken Tesfaw

በጀግናው ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ቤተሰቦች ላይ የደኅንነቶች ጫና ተባብሶ መቀጠሉ ተሰማ፡፡ የኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ የክስ ሒደት እየታየ የተዘጋጁ ምስክሮች ፍርድ ቤት ቃላቸውን በሚሰጡበት ሰዐት ሐምሌ 3 ቀን 2009 ዓ.ም. የአገዛዙ ደኅንነቶች የኮሎኔሉን የ5 ዓመት ሕጻን ልጅ ጠልፈው ለመውሰድ ሲሞክሩ በሕዝብ ርብርብ መክሸፉን በአካባቢው የነበሩ እማኞች ገልጸውልናል፡፡ እድሜያቸው በ20ዎቹ ውስጥ የሚገመቱ ወጣት የደኅንነት አባላት በዕለቱ ጠዋት ጀምሮ የኮሎኔል ቤተሰቦች በሚኖሩበት ቤት በር አካባቢ ቆመው መዋላቸውን የሚገልጹት ምንጮች ምን እንደሚፈልጉ ሲጠየቁ ‹‹ሰው እየጠበቅን ነው›› የሚል መልስ በትግርኛ ቅላጼ ባለው አማርኛ እንደመለሱላቸው ገልጸው ለረዥም ሰዐታት በአካባቢው መቆማቸው እንዳጠራጠሯቸው ተናግረዋል፡፡ ከሰዐት በኋላ የኮሌኔሉን ልጅ ጠልፈው ለመውሰድ በማባበል ላይ እያሉ የኮሎኔል ደመቀ የቅርብ ዘመድ የድረሱልኝ ጩኸት በማሰማቷ በአካባቢ የነበሩ ጥቂት ሰዎች ተሰባሰቡ፤ ከዚያም እነማን ናችሁ መታዎቂያ አሳዩን የሚል ጥያቄ ከተሰበሰቡት ጥቂት ወጣቶች ሲቀርብላቸው ወደ ማስፈራራት እንደገቡና በኋላ የሰው ቁጥር እየጨመረ ሲሔድ በተሸከርካሪ በፍጥነት መሰወራቸውን የዐይን እማኞች ገልጸዋል፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ ከሐምሌ 3 እስከ 5 ቀን 2009 ዓም ድረስ በኮሎኔል ላይ 9 የሚሆኑ የሰለጠኑ ምስክሮች ፍርድ ቤት ቀርበው መመስከራቸውን ሰምተናል፡፡ አብዛኛዎቹ ምስክሮች ከትግራይ ፊታቸውን ተሸፋፍነው በጥቁር መኪና በፖሊስ ታጅበው ፍርድ ቤት እንደገቡና ወዲያውኑ ወጥተው እንደተሰወሩ የፍርድ ሒደቱን የተከታተሉ ሰዎች ገልጸዋል፡፡ ዛሬ በዋለው ችሎት የዐማራ ልዩ ኃይል ፖሊስ ኃላፊ የነበረውና ሸፍቻለሁ በማለት ለአገዛዙ ሲሰራ የነበረው ኮማንደር ዋኘውን ጨምሮ እነ ኮማንደር ማሙየ መመስከራቸውን አውቀናል፡፡
የዐማራ ተጋድሎ አብሳሪው የጀግናው ኮሎኔል ደመቀ የፍርድ ሒደት ሆን ተብሎ የዐማራ ተጋድሎ አንደኛ ዓመት በሚታሰብበት ቀን እንደተደረገ የሚገልጹት ምንጮች የኮሎኔሉን ሞራል ለመጉዳት የታሰበ ቢሆንም ጀግናው ግን የበለጠ የተረጋጋና አስፈሪ ግርማ ሞገስን ተላብሶ እንደነበር ፍርድ ቤት የነበሩ ግለሰቦች ገልጸውልናል፡፡ 8 የመከላከያ ምስክሮች ከሐምሌ 25 እስከ 27 ቀን ድረስ እንዲቀርቡ ፍርድ ቤቱ አዟል

Friday, July 7, 2017

አማራውንና ኦሮሞውን ለመከፋፈል ወያኔ ያወጣው አዋጅን የኦሮሞ ድርጅቶች እየተቃወሙት ይገኛሉ source zehabesha

የፍኖተ ዴሞክራሲ ዜናና ኃተታ – 
#ርዕሰ ዜና

#ተመድ ከ800 ሺ ዜጎች በላይ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል አለ
#አነስተኛ ነጋዴዎች ከመጠን በላይ የተቆለባቸው ታክስ እያስመረራቸው ነው
#በአፍሪካ ቀንድና በየመን የተከሰተው የኮሌራ በሽታ ወደ አውዳሚ ደረጃ እየተዛወረ ነው
#እስራዔል የአፍርካ ስደተኞችን ሁኔታ አባባሰች ተባለ
#አማራውንና ኦሮሞውን ለመካፋፈል ወያኔ ያወጣው አዋጅ የኦሮሞ ድርጅቶች እየተቃወሙት ይገኛሉ
#የአፍሪካ ኅብረት መሪዎች ለቀ.ኃ.ሥ ሃውልት ለመስራት ሲወስን ወያኔ ለመለሰ ካልተሰራ በማለት እያስቸገረ ነው

##ዝርዝር ዜናዎች##
#የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ ባሰባሰባው መረጃ መሰረት በድርቁ ምክንያት በኢትዮጵያ 843ሺ ዜጎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በየመጠለያ ጣቢያዎች የሚኖሩ መሆናቸውን ገልጿል። 36,750 የሚሆኑ ዜጎች በኮሌራ በሽታ መያዛች ገልጾ ከዚሁ ውስጥ 780 መሞታቸውን መረጃ የደረሰው መሆኑን ይፋ አድርጓል፡፤ 110 680 የሚሆኑ ህጻናትም በተመጣጣኝ የምግብ እጥረት እየተሰቃዩ መሆናቸውና እስካሁን ድረስ የነበረው የበልግ መኸር በበርካታ አካባቢዎች በጣም አነስተኛ መሆኑን ገልጾ በዘንድሮ ክረምት በአንዳንድ አካባቢዎች ከአማካዩ ከፍ ያለ ዝናም መዝነሙ የተመዘገበ ቢሆንም በደቡብና በደቡብ ምስራቅ አካባቢዎች የጣለው ዝናም አነስተኛ በመሆኑ የረሃቡ ችግር ሊቀጥል እንደሚችል ይገመታል ብሏል።
#የቀን ገቢ ግምት በሚል ፈሊጥ የወያኔ አገዛዝ በማንአለብኝነት በአነስተኛ ነጋዴዎች ላይ የቆለለው ታክስ ብዙዎችን ያስቆጣና ያስመረረ መሆኑ ከዚህ በፊት የተዘገበ ሲሆን ታክሱ በዝቷል በሚል አቤቱታ በሚያቀርቡ ነጋዴዎች ላይ የአገዛዙ ባለስልጣኖች ማስፈራሪያና ማስጠንቀቂያ እየሰጡ መሆናቸው ተገልጸ። በነሲብና በማን አለብኛነት ይህን ያህል ገቢ አለህ፤ ይህን ያህል ታተርፋለህ በማለት በእያንዳንዱ ነጋዴ ላይ በዘፈቀደ የተቆለለው ታክስ አግባብ አይደለም በማለት ነጋዴዎቹ ቅሬታቸውን እያሰሙ ሲሆን በቡድን በመሆን ቅሬታ ማሰማት አይቻልም፤ ታክስ ሰብሳቢዎችን አመናጭቃችኋል ፤ አስፈራርታችኋል በማለት በነጋዴዎች ላይ ክስ መስርተውውባቸዋል። ነጋዴዎቹ በግለሰብ ደረጃ ቅሬታ እንዲያቀርቡ ቢነገራቸውም ታክሱን ከመክፈል እንደማይድኑም ታውቋል።
#በአፍሪካ ቀንድና በየመን ያለው የረሃብን የበሽታ የኮሌራ ወረርሽኝ ሁኔታ ከአስደንጋጭ ወደ አጥፊና አውዳሚ ደረጃ እየተሸጋገረ ነው ሲሉ ታዛቢዎች አስጠነቀቁ ። በደቡብ ሱዳን ባለው ቀውስ በመንግስት ግድ የለሽነት ሚሊዮኖች ለሞት አደጋ ተጋልጠዋል ያሉ ክፍሎች ኮሌራ በደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያና በየመን በመስፋፋት ላይ ነው ሲሉ ጠቁመዋል ። ወያኔን በመደገፍ የሀገር ኤኮኖሚ እያደገ ነው የሚሉ ክፍሎች በኢትዮጵያ የተከሰተውን ረሃብ አቅልለው እያቀረቡ ቢሆንም በአፋር፤ኦጋዴን፤ሰሜን ሸዋ ፤ደቡብ ኢትዮጵያ ወዘተ ረሃቡ መግደል ከጀመረ ውሎ አድሯል እየተባለም ነው ። የግልገል ግቤ 3 ግድብ አርሶ አደሮችን የሚያርሱት መሬት ማሳጣቱም ለችግሩ አስተዋጾ አድርጓል የተባለ ሲሆን ብዙ ሳይነገርለትም የተጀመረው የግልገል ግቤ 4 ግድብ ስራ በአካባቢውና አልፎም በኬንያ ችግር ፈጣሪ መሆኑ አይቀሬ መሆኑ ተዘግቧል ። እየተደበቀ ያለውን የአስከፊ ረሃብ ሁኔታ በዓለም አቀፍ ደረጃ ማጋለጥ የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው በሚልም ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
#በጨካኝና ዘረኛ ጸረ ስደተኛ አቅዋሟ ውግዘት የደረሰባት እስራኤል ከዓለም አቀፍ ትኩረት በተሸፈነ መንገድ የአፍሪካ ስደተኞችን መከራ አባብሳ ትገኛለች በሚል ተወገዘች ። ይህ ውግዘት የተመሰረተው እስራኤል የሱዳንና ኤርትራ ስደተኖችን በመደለልም ሆነ በማስገደድ ወደ ሩዋንዳ ኪጋሊ ወስዳ መጣል ላይ ስለተሰማራች ነው ተብሏል ። በምትሄዱበት ጥገኝነትን ታገኛላችሁ የሚባሉት ስደተኞች በኪጋሊ እንግልት እየደረሰባቸውና ከዚያም ወደ ዩጋንዳ በገንዘብ ክፍያ ተወስደው እንደሚጣሉ ሊታወቅ ተሏል ። እስካሁን እስራኤል ወደ 2 ሺ የሚጠጉ ስደተኞችን ማባረሯ ታውቋል ። የእስራኤል ባለስልጣኖች በአሳፋሪ ዘረኝነት የአፍሪካ ስደተኞችን ካንሰር በሽታ ብለው መሰየማቸውና ዘግናኝ ዘረኝነትንም ማንጸባረቃቸው የተሰማና የታየ ነው ያሉ ታዛቢዎች በዩጋንዳና ሩዋንዳ ስደተኞቹ መነገጃ ሆነው ለአስከፊ ስቃይ የተዳረጉ መሆናቸው ታውቋል ብለዋል ። እስራኤል ለርዋንዳና ዩጋንዳ የተወሰነ ገንዘብ ከፍላ ተጨማሪ ስደተኞችን ልታጓጉዝ ተዘጋጅታለችም ተብሏል ።
#ወያኔ ኦሮሞና አማራን መከፋፈል በሚለው መርሁ መሰረት በቅርቡ አዲስ አበባ ላይ ያወጣው መሰሪ አዋጅ በአብዛኛው የኦሮሞ ድርጅቶችና ቡድኖች በሰፊው የተወገዘ መሆኑ ተዘግቧል ። ኦሮሞዎችን በዚህ መንገድ ደልዬ እጠቀምባቸዋለሁ ብሎ በንቀት የተነሳው ወያኔ ከወዲሁ ዕቅዱ ስለከሸፈበት ልዩ ስብሰባ በከፍተኛ አመራር ደረጃ ማድረጉም ተጋልጧል ። ታዛቢዎች በማስተር ፕላን ሽፋን የሕዝብን መሬት ሊቀማ ተነስቶ የከሸፈበት ወያኔ በዚህ አዋጅም የሕዝብን መሬት በራሱ እጅ ሊያስገባ እንጂ ለማንኛውም ሕዝብ ሊጠቅም ተነስቶ አይደለም ሲሉ አጋልጠውታል ። የወያኔ ተንኮል ከወዲሁ ከሽፏል ሊባል ይቻላልም ተብሏል ። በመጪው የሕዝብ ቆጠራ ወያኔ አብዛኛው የአዲስ አበባ ነዋሪ ትግሬ ነው ብሎ እንደ ወልቃይት ጠገዴ ከተማይቷን የትግራይ ከማለት የሚመለስ አይደለም ሲሉ አንዳንድ ክፍሎች ተችተዋል ።
#በርካታ የአፍሪካ መሪዎችና የፖለቲካ ሀይሎች ከአፍሪካ ህብረት መስራቾች አንዱ ለሆኑት ለአጼ ኃይለስላሴ ሀውልት ይቁማላቸው ማለታቸው ታወቀ; ወያኔ በዚህ አስታኮ ለከሀዲውና የባዕዳን ቅጥረኛ ለሆነው ለመለስ ዜናዊም በተጽዕኖ ሀውልት ሊያቆም መወሰኑ ተወግዟል ። አጼው ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት መስራቾች አንዱ ሲሆኑ መለስ ዜናዊ ግን ለአፍሪካ የቆመ ሳይሆን ኢትዮጵያና አፍሪካን ለምዕራባውያን የሸጠና የኢምፔሪያሊዝም ቅጥረኛ የነበረ በመሆኑ ሀውልት ሊሰራለት ቀርቶ በጸረ አፍሪካነት መወገዝ ያለበት ከሀዲ ነው ሲሉ ብዙዎች በጥብቅ ተቃውመዋል።
#የአፍሪካውያን ቁጥር ጨምሯልና መቀነስ አለበት ባዩ የአሜሪካው የጠገበ ሀብታም ቢል ጌትስ ውድቅ የወያኔ የጤና ተቋሞችን ቢያዳንቅም ሆነ ድህነት በስተፋፋበት ሀገር ኤኮኖሚ ተመነደገ ተብሎ ቢዋሽም በተደረጉ ጥናቶች በወያኔ አገዛዝ ስር ትምህርት ሳይሆን ድንቁርና መስፋፋቱ ተጋልጧል ። አንደኛ ደረጃ ትምህርት ጨርሰው ማንበበና መጻፍ በሚገባው ደረጃ የማይችሉ ብዙዎች ናቸው ያሉ ክፍሎች በየእርከኑ የተመደቡ አስተማሪዎችም ቢሆን ብቃታቸው አጠያያቂ ነው ብለዋል ። ወያኔ ብቃይ ያላቸውን አስተማሪዎች መንጥሮ ማባረሩ አይረሳም ያሉ ክፍሎች የአስተማሪዎችንም ታሪካዊ ማህበር አፍርሶ ለዘረኛ ፖለቲካው በሚያመች ደረጃ ትምህርትን አዳክሟል ሲሉ ከሰዋል ። ይህ ሕዝብ ሁሉየሚያውቀው ሀቅ በባዕዳንም ጥናት ዛሬ እየተረጋገጠ በመሆን ውግዘት መቀበል የተገደደው ወያኔ በውሸቱ በመቀጠል ከ97 በመቶአ ያላነሱ ሕጻናት ትምህርት ቤት መግባታቸው ብቻ ሳይሆን ከዚህ በፊት ባልታየ ደረጃ የማንበብ መጻፍ ችሎታ ያለው ሕዝብ ቁጥር እጥፍ ድርብ ጨምሯል በሚል ቅጥረኞቹን እያስዋሸ ነው በሚልም ተጋልጧል ።
የፍኖተ ዴሞክራሲ ዜናና ኃተታ – ሰኔ 28 ቀን 2009 ዓ.ም. #ርዕሰ ዜና #ተመድ ከ800 ሺ ዜጎች በላይ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል አለ #አነስተኛ ነጋዴዎች ከመጠን በላይ የተቆለባቸው ታክስ እያስመረራቸው ነው #በአፍሪካ ቀንድና በየመን የተከሰተው የኮሌራ በሽታ ወደ አውዳሚ ደረጃ እየተዛወረ ነው #እስራዔል የአፍርካ ስደተኞችን ሁኔታ አባባሰች ተባለ #አማራውንና ኦሮሞውን ለመካፋፈል ወያኔ ያወጣው አዋጅ የኦሮሞ ድርጅቶች እየተቃወሙት ይገኛሉ #የአፍሪካ ኅብረት መሪዎች ለቀ.ኃ.ሥ ሃውልት ለመስራት ሲወስን ወያኔ ለመለሰ ካልተሰራ በማለት እያስቸገረ ነው ##ዝርዝር ዜናዎች## #የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ ባሰባሰባው መረጃ መሰረት በድርቁ ምክንያት በኢትዮጵያ 843ሺ ዜጎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በየመጠለያ ጣቢያዎች የሚኖሩ መሆናቸውን ገልጿል። 36,750 የሚሆኑ ዜጎች በኮሌራ በሽታ መያዛች ገልጾ ከዚሁ ውስጥ 780 መሞታቸውን መረጃ የደረሰው መሆኑን ይፋ አድርጓል፡፤ 110 680 የሚሆኑ ህጻናትም በተመጣጣኝ የምግብ እጥረት እየተሰቃዩ መሆናቸውና እስካሁን ድረስ የነበረው የበልግ መኸር በበርካታ አካባቢዎች በጣም አነስተኛ መሆኑን ገልጾ በዘንድሮ ክረምት በአንዳንድ አካባቢዎች ከአማካዩ ከፍ ያለ ዝናም መዝነሙ የተመዘገበ ቢሆንም በደቡብና በደቡብ ምስራቅ አካባቢዎች የጣለው ዝናም አነስተኛ በመሆኑ የረሃቡ ችግር ሊቀጥል እንደሚችል ይገመታል ብሏል። #የቀን ገቢ ግምት በሚል ፈሊጥ የወያኔ አገዛዝ በማንአለብኝነት በአነስተኛ ነጋዴዎች ላይ የቆለለው ታክስ ብዙዎችን ያስቆጣና ያስመረረ መሆኑ ከዚህ በፊት የተዘገበ ሲሆን ታክሱ በዝቷል በሚል አቤቱታ በሚያቀርቡ ነጋዴዎች ላይ የአገዛዙ ባለስልጣኖች ማስፈራሪያና ማስጠንቀቂያ እየሰጡ መሆናቸው ተገልጸ። በነሲብና በማን አለብኛነት ይህን ያህል ገቢ አለህ፤ ይህን ያህል ታተርፋለህ በማለት በእያንዳንዱ ነጋዴ ላይ በዘፈቀደ የተቆለለው ታክስ አግባብ አይደለም በማለት ነጋዴዎቹ ቅሬታቸውን እያሰሙ ሲሆን በቡድን በመሆን ቅሬታ ማሰማት አይቻልም፤ ታክስ ሰብሳቢዎችን አመናጭቃችኋል ፤ አስፈራርታችኋል በማለት በነጋዴዎች ላይ ክስ መስርተውውባቸዋል። ነጋዴዎቹ በግለሰብ ደረጃ ቅሬታ እንዲያቀርቡ ቢነገራቸውም ታክሱን ከመክፈል እንደማይድኑም ታውቋል። #በአፍሪካ ቀንድና በየመን ያለው የረሃብን የበሽታ የኮሌራ ወረርሽኝ ሁኔታ ከአስደንጋጭ ወደ አጥፊና አውዳሚ ደረጃ እየተሸጋገረ ነው ሲሉ ታዛቢዎች አስጠነቀቁ ። በደቡብ ሱዳን ባለው ቀውስ በመንግስት ግድ የለሽነት ሚሊዮኖች ለሞት አደጋ ተጋልጠዋል ያሉ ክፍሎች ኮሌራ በደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያና በየመን በመስፋፋት ላይ ነው ሲሉ ጠቁመዋል ። ወያኔን በመደገፍ የሀገር ኤኮኖሚ እያደገ ነው የሚሉ ክፍሎች በኢትዮጵያ የተከሰተውን ረሃብ አቅልለው እያቀረቡ ቢሆንም በአፋር፤ኦጋዴን፤ሰሜን ሸዋ ፤ደቡብ ኢትዮጵያ ወዘተ ረሃቡ መግደል ከጀመረ ውሎ አድሯል እየተባለም ነው ። የግልገል ግቤ 3 ግድብ አርሶ አደሮችን የሚያርሱት መሬት ማሳጣቱም ለችግሩ አስተዋጾ አድርጓል የተባለ ሲሆን ብዙ ሳይነገርለትም የተጀመረው የግልገል ግቤ 4 ግድብ ስራ በአካባቢውና አልፎም በኬንያ ችግር ፈጣሪ መሆኑ አይቀሬ መሆኑ ተዘግቧል ። እየተደበቀ ያለውን የአስከፊ ረሃብ ሁኔታ በዓለም አቀፍ ደረጃ ማጋለጥ የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው በሚልም ማሳሰቢያ ተሰጥቷል። #በጨካኝና ዘረኛ ጸረ ስደተኛ አቅዋሟ ውግዘት የደረሰባት እስራኤል ከዓለም አቀፍ ትኩረት በተሸፈነ መንገድ የአፍሪካ ስደተኞችን መከራ አባብሳ ትገኛለች በሚል ተወገዘች ። ይህ ውግዘት የተመሰረተው እስራኤል የሱዳንና ኤርትራ ስደተኖችን በመደለልም ሆነ በማስገደድ ወደ ሩዋንዳ ኪጋሊ ወስዳ መጣል ላይ ስለተሰማራች ነው ተብሏል ። በምትሄዱበት ጥገኝነትን ታገኛላችሁ የሚባሉት ስደተኞች በኪጋሊ እንግልት እየደረሰባቸውና ከዚያም ወደ ዩጋንዳ በገንዘብ ክፍያ ተወስደው እንደሚጣሉ ሊታወቅ ተሏል ። እስካሁን እስራኤል ወደ 2 ሺ የሚጠጉ ስደተኞችን ማባረሯ ታውቋል ። የእስራኤል ባለስልጣኖች በአሳፋሪ ዘረኝነት የአፍሪካ ስደተኞችን ካንሰር በሽታ ብለው መሰየማቸውና ዘግናኝ ዘረኝነትንም ማንጸባረቃቸው የተሰማና የታየ ነው ያሉ ታዛቢዎች በዩጋንዳና ሩዋንዳ ስደተኞቹ መነገጃ ሆነው ለአስከፊ ስቃይ የተዳረጉ መሆናቸው ታውቋል ብለዋል ። እስራኤል ለርዋንዳና ዩጋንዳ የተወሰነ ገንዘብ ከፍላ ተጨማሪ ስደተኞችን ልታጓጉዝ ተዘጋጅታለችም ተብሏል ። #ወያኔ ኦሮሞና አማራን መከፋፈል በሚለው መርሁ መሰረት በቅርቡ አዲስ አበባ ላይ ያወጣው መሰሪ አዋጅ በአብዛኛው የኦሮሞ ድርጅቶችና ቡድኖች በሰፊው የተወገዘ መሆኑ ተዘግቧል ። ኦሮሞዎችን በዚህ መንገድ ደልዬ እጠቀምባቸዋለሁ ብሎ በንቀት የተነሳው ወያኔ ከወዲሁ ዕቅዱ ስለከሸፈበት ልዩ ስብሰባ በከፍተኛ አመራር ደረጃ ማድረጉም ተጋልጧል ። ታዛቢዎች በማስተር ፕላን ሽፋን የሕዝብን መሬት ሊቀማ ተነስቶ የከሸፈበት ወያኔ በዚህ አዋጅም የሕዝብን መሬት በራሱ እጅ ሊያስገባ እንጂ ለማንኛውም ሕዝብ ሊጠቅም ተነስቶ አይደለም ሲሉ አጋልጠውታል ። የወያኔ ተንኮል ከወዲሁ ከሽፏል ሊባል ይቻላልም ተብሏል ። በመጪው የሕዝብ ቆጠራ ወያኔ አብዛኛው የአዲስ አበባ ነዋሪ ትግሬ ነው ብሎ እንደ ወልቃይት ጠገዴ ከተማይቷን የትግራይ ከማለት የሚመለስ አይደለም ሲሉ አንዳንድ ክፍሎች ተችተዋል ። #በርካታ የአፍሪካ መሪዎችና የፖለቲካ ሀይሎች ከአፍሪካ ህብረት መስራቾች አንዱ ለሆኑት ለአጼ ኃይለስላሴ ሀውልት ይቁማላቸው ማለታቸው ታወቀ; ወያኔ በዚህ አስታኮ ለከሀዲውና የባዕዳን ቅጥረኛ ለሆነው ለመለስ ዜናዊም በተጽዕኖ ሀውልት ሊያቆም መወሰኑ ተወግዟል ። አጼው ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት መስራቾች አንዱ ሲሆኑ መለስ ዜናዊ ግን ለአፍሪካ የቆመ ሳይሆን ኢትዮጵያና አፍሪካን ለምዕራባውያን የሸጠና የኢምፔሪያሊዝም ቅጥረኛ የነበረ በመሆኑ ሀውልት ሊሰራለት ቀርቶ በጸረ አፍሪካነት መወገዝ ያለበት ከሀዲ ነው ሲሉ ብዙዎች በጥብቅ ተቃውመዋል። #የአፍሪካውያን ቁጥር ጨምሯልና መቀነስ አለበት ባዩ የአሜሪካው የጠገበ ሀብታም ቢል ጌትስ ውድቅ የወያኔ የጤና ተቋሞችን ቢያዳንቅም ሆነ ድህነት በስተፋፋበት ሀገር ኤኮኖሚ ተመነደገ ተብሎ ቢዋሽም በተደረጉ ጥናቶች በወያኔ አገዛዝ ስር ትምህርት ሳይሆን ድንቁርና መስፋፋቱ ተጋልጧል ። አንደኛ ደረጃ ትምህርት ጨርሰው ማንበበና መጻፍ በሚገባው ደረጃ የማይችሉ ብዙዎች ናቸው ያሉ ክፍሎች በየእርከኑ የተመደቡ አስተማሪዎችም ቢሆን ብቃታቸው አጠያያቂ ነው ብለዋል ። ወያኔ ብቃይ ያላቸውን አስተማሪዎች መንጥሮ ማባረሩ አይረሳም ያሉ ክፍሎች የአስተማሪዎችንም ታሪካዊ ማህበር አፍርሶ ለዘረኛ ፖለቲካው በሚያመች ደረጃ ትምህርትን አዳክሟል ሲሉ ከሰዋል ። ይህ ሕዝብ ሁሉየሚያውቀው ሀቅ በባዕዳንም ጥናት ዛሬ እየተረጋገጠ በመሆን ውግዘት መቀበል የተገደደው ወያኔ በውሸቱ በመቀጠል ከ97 በመቶአ ያላነሱ ሕጻናት ትምህርት ቤት መግባታቸው ብቻ ሳይሆን ከዚህ በፊት ባልታየ ደረጃ የማንበብ መጻፍ ችሎታ ያለው ሕዝብ ቁጥር እጥፍ ድርብ ጨምሯል በሚል ቅጥረኞቹን እያስዋሸ ነው በሚልም ተጋልጧል ።

Thursday, July 6, 2017

በባህርዳር መግቢያ መውጫወች በተለይ በጎንደር መስመር ከፍተኛ ወታደራዊ ፍተሻ እየተደረገ ነው !! source satenewa

ይህ የወያኔ ፍተሻ የሚያገኘው ነገር ኖሮ ሳይሆን በህዝቡ ላይ የፍርሃት ቆፈን በመጫን የስነ ልቦና ጫና ለመፍጠር ያለመ ነው። ህወሓት /ወያኔ ውርደቱን ለመሸፋፈን ያዙኝ ልቀቁኝ አብዝቷል። የደረሰበት መተረማመስና መፈረካከስ ተረጋግቶ እንዲቀመጥ አላደረገውም። የነፃነት ሃይሎች ያልተጠበቀና ምንም መረጃ ባልወጣበት የሚፈፀም ጥቃት ፋታ ነስቶታል። ወደ ጎጃም እየገሰገሰ የሚገኘው የነፃነት ትግል ፋና የውስጡን አለመረጋጋት እና ጎራ ለይቶ እርስ በርሱ በጥርጣሬ መተያየቱን በጉልህ ጥርሱን አግጥጦ እንዲታይ አድርጎታል። በባህርዳር አየር ማረፊያ የተያዘው ተቀጣጣይ ፈንጂ ደግሞ የነፃነት ትግሉ አድማሱን ማስፋቱና ከእጁ እየወጣ የሚገኘው የቀጠናው የነፃነት ታጋዩች እንቅስቃሴ በወታደር ብዛት መግታት እንዳልቻለ ያረጋገጠ ትልቅ ስጋት ሁኖበታል።በዚህም የራሴ የሚላቸውን ሰወች በመጠራጠር እስከ ማሰር እንደደረሰ መረጃወች ይጠቁማሉ። በቀጣይ ይደርስብኛል ብሎ ከሰጋቸው አንኳር ጥቃቶች በመነሳት በለሊት ማንኛውንም የስራ መኪና እንቅስቃሴ በሰሜኑ ቀጠና እስከማገድ እና በኬላወች ለፍተሻ በማስቆም እንዲያድር ያደርጋሉ። በዛሬ ዕለተ ረዕቡ ሰኔ 28/2009 ዓ.ም አነጋግ የጀመረው ፍተሻ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች (ባለማዕረግተኞች)በስምሪት የተሳተፉበት ነበር። በትናንትናው ምሽት በበግ ተራ አካባቢ ሰወች እየታደኑ ይያዙ እንደነበር የአይን እማኞች ይናገራሉ። በወታደሮች እየተያዙ የተወሰዱ ሰወች ትክክለኛ ማንነትና ቁጥር እስካሁን ለማረጋገጥ አልተቻለም። ይህ በህወሓት ወንበዴ ቡድን የሚፈፀም ድንገተኛ የተጋነነ ወታደራዊ ሰልፍና ፍተሻ በመውጫ መግቢያወች ምንም የሚያገኘው ኑሮ ሳይሆን በነዋሪው ህዝብ ላይ የፍርሃት ቆፈን በመደረብ የስነ ልቦና ጫና ለመፍጠር ያለመ ውርደቱን መሸፈኛ ካባ ነው ። ስነልቦናው እንደ አለት በጠነከረ ህዝብ ላይ ጫና ለመፍጠር መሯሯጥ ትርፉ መላላጥ ብቻ ነው። ድል ድል ይሸታል አየሩ ፣ ትርምስምስ ብሏል ጠላት መንደሩ ። ድል ምንጊዜም የህዝብ ነው !! @እንቅዩጳዝዩን የአርበኞቹ ልጂ     

” እኛን ሰዎች ኤርትራን ሸጣችኋታል እያሉ ያሙናል፡፡ ” ኃይለማርያም ደሳለኝ source bbn

ጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም እስራኤልን ብቻ መጎብኘታቸው ቅር እንዳሰኛቸው የፍልስጤሙ መሪ ተናገሩ . BBN.

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ፍልስጤምን አለመጎብኘታቸው ቅሬታ እንደፈጠረባቸው የፍልስጤሙ መሪ ተናገሩ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአንድም ሁለት ጊዜ እስራኤልን መጎብኘታቸውን ያስታወሱት የፍልስጤሙ መሪ መሐሙድ አባስ፣ ፍልስጤምን አለመጎብኘታቸውም ቅር እንዳሰኛቸው ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደነገሯቸው ሪፖርተር ዘግቧል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩን የእስራኤል ጉብኝት ተከትሎ፣ ፍልስጤም የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በተለየ ሁኔታ እየተከታተለችው እንደምትገኝም የፍልስጤሙን መሪ ጠቅሶ ጋዜጣው ዘግቧል፡፡
ሁለቱ መሪዎች የተነጋገሩት በአዲስ አበባ ሲደረግ በነበረው የአፍሪካ መሪዎች ጉባኤ ኢ-መደበኛ በሆነ ውይይት ላይ ሲሆን፣ በውይይቱም ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ተደጋጋሚ ወቀሳ ቀርቦባቸዋል፡፡ ከዚህ ቀደም ፍልስጤም ባቀረበችው ግብዣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ሀገራቸውን እንዲጎበኙ የቀረበላቸውን ተደጋጋሚ ግብዣ አለመቀበላቸው ቅር እንዳሰኛቸው የፍልስጤሙ መሪ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ኢትዮጵያን እንደ አገሬ ነው የማያት፡፡›› ያሉት ፕሬዚዳንት መሐሙድ አባስ፣ ‹‹ከእስራኤል ፕሬዚዳንት ቤኒያሚን ኔታንያሁ ጋር ያለው ችግር የአገሬን ሉዓላዊነትና ደኅንነት እየተፈታተ ነው፡፡›› ማለታቸውንም ዘገባው አመልክቷል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያ ደሳለኝ ከዚህ ቀደም እስራኤልን የጎበኙት በግላቸው መሆኑን ለፍልስጤሙ መሪ የገለጹላቸው ሲሆን፣ ‹‹ፍልስጤምን መጎብኘት አለመቻሌን ከእስራኤል ጋር አታያይዙት፡፡›› ብለዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም በቅርቡ እንኳን ወደ እስራኤል አቅንተው የነበሩት መንግስታቸውን ወክለው እንደነበር አይዘነጋም፡፡ ሆኖም ‹‹ወደ እስራኤል የሔድኩት በግሌ ነው፡፡›› ማለት ለምን እንደፈለጉ አልታወቀም፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም ‹‹ኢትዮጵያ ከፍልስጤም ጋር ያላትን ግንኙነት ወደፊት ታጠናክራለች፡፡›› ብለዋል፡፡
አቶ ኃይለ ማርያም ንግግራቸውን ቀጥለው በውይይቱ ላይ ‹‹እኛን ሰዎች ኤርትራን ሸጣችኋታል እያሉ ያሙናል፡፡ እውነታው ግን የሕዝብ ውሳኔ ነው፡፡›› ካሉ በኋላ፣ ‹‹እናንተም ሕዝቦቻችሁን መሠረት አድርጋችሁ በመካከላችሁ ያለውን ግጭት መፍታት ይገባችኋል፡፡›› ሲሉ ለፍልስጤሙ መሪ መሐሙድ አባስ ምክር ቢጤ ለግሰዋል፡፡ መሐሙድ አባስ በበኩላቸው፣ ሀገራቸው ከእስራኤል ጋር ያላትን ቅራኔ ለመፍታት ከአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ውይይት እያደረጉ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን፣ አቶ ኃይለማርያም በበኩላቸው ‹‹በአሜሪካ ፕሬዚዳንት ውሳኔ ዘላቂነት ላይ ጥርጣሬ ቢኖረኝም ጅምሩ ጥሩ ነው፡፡›› ብለዋል፡፡
BBN

Tuesday, July 4, 2017

“ነጭ ኑግ ጥቁር ወተት ውለዱ” – 25 አመታት የሌላውን ሁሉ ውጣ የማትጠረቃው ክልል! ! [ቬሮኒካ መላኩ] source zhebesha

ትናንት ነበር ሌላም ጊዜ እንደማደርገው ለአመታት የጆሮዬ ጓደኛ የሆነውን የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ሰአቱን ጠብቄ ከፍቸው ነበር። የእለቱ የራዲዮ ፕሮግራሙ አስተዋዋቂ ” አድማጮቻችን በዛሬው የፕሮግራማችን ሁለተኛ ክፍል ላይ ኢትዮጵያ በኤርትሪያ ላይ የምትከተለው ፖሊሲ በትግራይ ክልል እየፈጠረ ያለውን ችግር የሚያስረዱ ሁለት እንግዶች ስለሚቀርቡ ይሄን ዝግጅት እንድታዳምጡ እንጋብዛለን> > በማለት ፕሮግራሙን አስተዋወቀ። እኔም ሰአቱን ጠብቄ ፕሮግራሙን መከታተል ጀመርኩኝ ። … የፕሮግራሙ አዘጋጅ የሆነችው አንጋፋዋ ጋዜጠኛ አዳነች ፍስሃዬ ስትሆን የጋበዘቻቸው ሰዎች ደሞ ከወደ ትግራይ እንደሆኑ በሚናገሩት አማርኛ በደንብ መረዳት ይቻል ነበር። ሲጀመር ይሄ ፕሮግራም መቅረብ የነበረበት በቪኦኤ የትግርኛ ፕሮግራም ነበር በአማርኛው ክፍለ ጊዜም ይቅረብ ከተባለ ቢያንስ አንድ አይነት አመለካከት ፣አንድ አይነት አስተሳሰብ ያላቸውን እንግዶች ከማቅረብ በጉዳዩ ላይ የተለየ አመለካከት ያላቸው እንግዶች ቢቀርቡ ፕሮግራሙን ሚዛናዊ ማድረግ ይቻል ነበር። … በነገራችን ላይ አንጋፋውና ተወዳጁ የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ በአንድ ክልል እና ብሄር የእጅ አዙር ቁጥጥር ስር የገባ ይመስላል። ቪኦኤ ከሌላው የኢትዮጵያ ክፍል በተለየ ከትግራይ ክልል የሚዘግብ ዘጋቢ አለው ፣ በትግሪኛ ቋንቋ የሚያሰራጨው በክልሉ ፖለቲካዊ ፣ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና እና ሌሎች ጉዳዮች ብቻ አትኩሮ የሚሰራ የ30 ደቂቃ ፕሮግራም አለው ። ይሄ ሁሉ አልበቃ ብሎ የአማረኛውም ፕሮግራም ብዙ ጊዜውን የሚያጠፋው ስለትግራይ በመዘገብ ነው። … ወደ ዋናው የትናንቱ የቪኦኤ ፕሮግራም ይዘት ስገባ ፕሮግራሙ በሁለት ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር: ። በፕሮግራሙ የቀረቡት እንግዶች ጥያቄያቸውን ለጠ/ሚ ሀይለማሪያምና ፌደራል መንግስት ማቅረባቸውንና በጎ ምላሽ እንደሚጠብቁ ገልፀዋል … ሁለቱ የፕሮግራሙ ይዘቶች … 1~ ትግራይ የጦርነት ቀጠና ሆና በልማት እየተጎዳች ስለሆነ ከፌደራል መንግስት ድጎማ እንድደረግላት የሚጠይቅ ሲሆን… … 2~ ኢትዮጵያ በኤርትራ ላይ የምትከተለው No war No peace ፖሊሲ ተቀይሮ ወደ ጦርነት እንድገባ የሚገፋፋ አንድምታ ያለው ነው ። … በሁለቱም ጉዳዮች ላይ ያለኝን አመለካከት አጠር በማድረግ ላስቀምጥ: ….. 1~ “ትግራይ በልማት እየተጎዳች በመሆኑ የፌደራል መንግስት ድጎማ ያስፈልጋታል ” ….. እንግሊዛዊው ባለቅኔና ገጣሚ ዊሊያም ሸክስፒር ” ሀምሌት ” በተባለው ዘመን አይሽሬ ተውኔቱ የሰውን ስግብግብነት ፣ አልጠግብ ባይነት ፣ክፋት ፣ ተንኮል እና ፈጣጣነት በአንድ አረፍተ ነገር ገልፆት ነበር … << O shame, where is thy blush ? Proclaim no shame !! …>> ” ሃፍረት ሆይ !! ይሉኝታ ቢስ ሆይ!! ቅላትሽ ወደት አለ? … አንተ ሀፍረተ ቢስ!! እናንተ ይሉኝታ የለሾች! ! ሃፍረት የሌለህ እንደሆንከ አዋጅ ተናገር >> እያለ ይቀጥላል ። እዚህ ላይ የዊሊያም ሸክስፒርን አባባል መጥቀሴ ለእነዚህ ሰዎች ተገቢና ገላጭ አባባል ሆኖ ስላገኘሁት ነው ። … ይች ኢትዮጵያ የምትባል አገር እስከ መቼ ነው የትግራይ ጥገት ላም ሆና የምትኖረው? አሁንም ከመቶ ሚሊዮን ህዝብ አፍ ላይ ተነጥቆ የእነሱ ክልል እንደ ታይዋን እና ሆንግ ኮንግ እንደሆን ይፈልጋሉ ። ብዙዎች በየቀኑ ከኢትዮጵያዊነት መንበር ሸርተት እያሉ ለመሸፈታቸው ዋናው ምክንያት ” ትግሬ እያጋበሰ የሚኖርባት እና ሌላው በችጋር ተጠብሶ የሚያለቅስባት አገር ፣ የተለያዩ ዜጎች እና ክልሎች በእኩል አይን የማይታዩበታ አገር አታስፈልገኝም ” በማለት ነው። ዛሬ የኢትዮጵያ ሌላው ክልል ዜጎች በርሃብ ፣ በእርዛት ፣ በእስር እና በግድያ የሚሰቃዩባት የትራጂዲያ መድረክ ናት ። እንደ ተራ እንስሳ በመከራ የሚጠበሱ ዜጎች ባሉባት አገር ውስጥ የአንድ ክልል ነዋሪዎች ሌላውን ህዝብ << ጥቁር ወተት እና ነጭ ኑግ ውለድ! >> የሚባለው የአልጠግብ ባዮች ልፈፋ በአስቸኳይ መቆም አለበት ። ቪኦኤስ እንደት ስራ ቢያጣ ነው ይሄን አይነት የለየለት የዘረፋ ፕሮጀክት ሊያቀርብልን የቻለው ? የኢትዮጵያ ምዝብርና ግፉእ ህዝብ ለ25 አመታት የተበዘበዘውና የተመዘበረው አንሶ አሁንም አመታት ቢውጡ ከርሳቸው የማይሞላና የማይጠግቡ ቡድኖች ሲሳይ መሆኑ ማብቃት አለበት ። ይሄ ካልሆነ ግን በአገራችን ይሄ አይነት ሰፍሳፋነትና አልጠግብ ባይነት እስካለ ድረስ በአገራችን ሰላም ሊሰፍን አይችልም ። … 2~ የኢትዮጵያ መንግስት በኤርትሪያ ላይ የሚከተለውን ፖሊሲ በመቀየር አስቸኳይ እርምጃ እንድወስድ ። … በሁለተኛ ደረጃ የአዳነች ፍስሃዬ እንግዶች ያስረዱትና እና ለፌደራል መንግስት አቀረብነው ያሉት ጉዳይ ” ጦርነት ይደረግልን” የሚል አንድምታ ይመስላል። ሀበሻ ሲተርት ” የዘንዶ ጉድጓድ በሞኝ ክንድ ይለካል ” ይላል። እነዚህ ሰዎች እቤታቸው ያለውን የዘንዶ ጉድጓድ በሌላው ኢትዮጵያዊ ክንድ ይለካልን እያሉ እየጠየቁ ይመስላል ። ከአመታት በፊት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ወጣት ወንዶች ከሞቀ ቤታቸው ወጥተው ወደ ጦር ሜዳ ዘመቱ። እነዚህ ወጣቶች ወደ ጦርነቱ ሆ ብለው የገቡት በወቅቱ ገንኖ በነበረው የብሔራዊ ስሜት ማዕበል ተነድተው እና አገራችን ተወረረች ብለው ነበር ።ይሁንና ብዙም ሳይቆይ ተገኘ የተባለው ድል ወደ ምሬት ተለወጠ። ሰዎች በዘር እየተለዩ እየተመረጡ የፈንጅ ማምከኛ እንደሆኑ ተረጋገጠ ።ምሽግ ውስጥ ሆነው የሚዋጉት ወታደሮች ብዙም ሳይቆይ እውነታው ግልጽ ሆነላቸው። የፖለቲካ መሪዎች ጉድ እንዳደረጓቸው፣እንዳታለሏቸውና የጦር መሪዎቻቸውም አሳልፈው እንደሰጧቸው ተረዱ። … ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ወጣቶች “ደስ እያላቸውና በፈቃደኝነት” ለጦርነት የዘመቱት ወድያውኑ ዘመቻው አንድን ቡድን የበላይነት ለመጠበቅ እንደሆነ ተረዱ ። ህዝቡም አወቀ ።የጦርነቱ ነጋሪት ጎሳሚዎች ጦርነት መኖር ያለበት “ተፈጥሮአዊ ግዴታ” ነው ብለው ያመኑ ይመስሉ ነበር ። BBC በተባለው የዜና ማሰራጫ “Human Wave ” በተባለው የጦርነት ስልት ያለቁትን ብሄሮች ስንሰማ የወያኔ መሪዎች ፊል ዊልያምስ የተባሉት ደራሲ “ማህበራዊ ዳርዊኒዝም” ጦርነት የተወሰኑ ዘሮችን ፣ ብሄሮችን ለማስወገድ” የሚያስችል ትክክለኛ መሣሪያ ነው የሚለውን አስተሳሰብ ተከታዮች እንደነበሩ ተረድተናል ። … ዛሬስ እነዚህ ሰዎች ምን አድርጉ እያሉን ነው? የምን ነጋሪት እየጎሰሙብን ነው? የማሰብ ችሎታ ያላቸው ሰዎች . . . እንዲህ ያለውን እብደት ሊቀበሉ ይችላሉ ወይ? በእርግጥ ዛሬ ሌላ ቀን ነው ። በእርግጥ ልንማረው የሚገባ አንድ ግልጽ ትምህርት አለ። ባለፉት አመታትት የታዩት አሳዛኝ ሁኔታዎች እንዳይደገሙ ከተፈለገ ሊሳሳቱ ከሚችሉት የሰው ልጆች ፍልስፍናዎች ይበልጥ አስተማማኝ የሆነ መመሪያ ያስፈልገናል። ከታሪክ መማር ። “ሰዎች ከታሪክ ሊማሩ ቢችሉ ኖሮ እንዴት ያለ ትምህርት ይገኝ ነበር! ነገር ግን በስሜታዊነትና በወገናዊነት ታውረናል። ተሞክሮ የፈነጠቀልን ብርሃን የጋን ውስጥ መብራት ሆኖብናል!”— ሳሙኤል ቴይለር ኮልሪጅ እንግሊዛዊው ባለቅኔ ሳሙኤል ኮልሪጅ በሰጠው አስተያየት እኔ እስማማለሁ ። ለአንድ የተወሰነ ዓላማ

Sunday, July 2, 2017

ሁከት አንስተዋል የተባሉ እስረኞች ከቅሊንጦ እስር ቤት ወደ ሌሎች እስር ቤቶች ተዛወሩ source zhabesha

file photo
የፍኖተ ዴሞክራሲ ዜናና ኃተታ –
ርዕሰ ዜና

#ሁከት አንስተዋል የተባሉ እስረኞች ከቅሊንጦ እስር ቤት ወደ ሌሎች እስር ቤቶች ተዛወሩ
#አመጽ ቀስቃሽ ግጥሞችን በዩቲዩብ አሰራጭተዋል የተባሉ ጋዜጠኞች ክስ ተመሰረተባቸው
#በጎንደር አንድ የሞርታር ጥይት ፈንድቶ በህይወትና በአካል ላይ ጉዳት አደረሰ
#ሳኡዲ አረቢያ የጣለችውን የቀን ገደብ ለ30 ቀን አራዘመች
#በአገራችን የገባው የተምች መንጋ በከፍተኛ ፍጥነት መስፋፋቱ አሳሳቢ ነው ተባለ
##ዝርዝር ዜናዎች##

#በቅሊንጦ ከሚገኘው የወያኔ እስር ቤት ውስጥ ከ20 የሚበልጡ እስረኞች ወደ ዘዋይ እስር ቤት ቁጥራቸው ያልታወቀ ሌሎች ደግሞ ወደ ሸዋ ሮቢት የተዛወሩ መሆኑ ታውቋል። እስረኞቹ ወደ ሌሎች እስር ቤቶች የተዛወሩበት ምክንያት በመካከላቸው በዘር ላይ የተሰመረተ ግጭት ፈጥረው ሁከት በማስነሳታችው ነው የሚል ምክንያት እየተሰጠ ሲሆን ከተዛወሩት መካከልም ከዚህ በፊት #እስር ቤቱን በማቃጠል የተከሰሱ እንዳሉበት ለማወቅ ተችሏል። ላለፉት ጥቂት ቀናት በቅሊንጦ እስር ቤት ዞን 4 እና 5 ውስጥ የታሰሩ እስረኞች ዘመዶቻቸው እንዳያዩዋቸው የተከለከሉ መሆናቸውም ታውቋል። እስር ቤት ውስጥ የታጨቀው እስረኛ በጣም በርካታ ከመሆኑ የተነሳ እስረኞች በጥበቱ የተማረሩ መሆናቸውን በተደጋጋሚ መግለጻችው ይታወቃል። በ 900 ሚሊዮን ብር እየተሰራ ነው የሚባለውም እስር ቤት ምን ያህል ችግሩን ሊያቃልል እንደሚችል አልታወቀም ተብሏል።
#በጋዘጠኛነት ሙያ ተሰማርተው የነበሩና አመጽ ቀስቃሽ ግጥሞችን በዩቱዩብ አሰራጭታችኋል የተባሉ ሰባት ሰዎች ክስ የተመሰረተባችው መሆኑ ታወቀ። ሰባቱ በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት ቀርበው የተሰነሰዘረባቸው ክስ የተሰማ ሲሆን ከተከሳሾች በኩል የሚቀርበውን የመጀመሪያ የመቃወሚያ ሀሳቦችን ለመሰማት ለሐምሌ 7 ቀን ቀጠሮ የተያዘ መሆኑ ታውቋል።
#በጎንደር ከተማ ቅዳሜ ከተማ ውስጥ ልዩ ስሙ አሮጌ ብረት ተራ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ የሞርታር ጥይት በመፈንዳቱ ምክንያት ሁለት ስዎች ህይወታቸውን ያጡ መሆናቸውና ሌሎች ሶስት ሰዎች የቆሰሉ መሆናችው ተነገረ። የሞርታር ጥይቱን ለብረት ሙቀጫ ለማዋል በብረት መጋዝ በመቁረጥ ላይ እንዳሉ ጥይቱ በመፈንዳቱ ሰዎቹ ወዲያውኑ ሊሞቱ የቻሉ መሆናቸው ተነግሯል።
#የሳኡዲ አረቢያ መንግስት ህገ ወጥ ናቸው የሚላቸው ስደተኞች ከአገሩ እንዲወጡ አውጆት የነበረውን የቀን ገደብ ለ 30 ቀናት ያራዘመው መሆኑን ገለጸ። ለቀን ገደቡ መራዘም በሳኡዲ መንግስት በኩል የተሰጠ ማብራሪያ ባይኖርም የወያኔ አገዛዝ እና አንዳንድ ወገኖች ላቀረቡት ጥያቄ የተሰጠ መልስ ሳይሆን አይቀርም የሚል ግምት አለ። በሳኡዲ አረቢያ ከ400000 እስከ 450000 ሺ የሚገመቱ ኢትዮጵያን ስደተኞች በህገ ወጥ መንገድ ይኖራሉ ተብሎ ሲገመት እስካሁን የተመለሱት ቁጥር ከ45000 እንደማይበልጥና የመጓጓዣ ሰነድ ተሰጥቷቸዋል የተባሉት 111 ሺ ብቻ መሆናቸው ተነግሯል።
#በአገራችን የገባው የተምች መንጋ በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ በመሄዱ ሁኔታው በጣም አሳሳቢ መሆኑ ተነገረ። እስካሁን ድረስ በ35 ዞኖች በ136 ሺ ሄክታር መሬት ላይ የተዘሩ ሰብሎችን ያበላሸው ይኽው የተምች መንጋ በቅርቡ እስከሁለት ሚሊዮን ሄክታር በሚድርስ ቦታዎች ላይ የተዘሩትን አዝርዕት ሊያበላሽ እንደሚችል ተገምቷል። ይኽም በአገሪቱ ውስጥ ለእርሻ ተስማሚ ከሆኑ መሬቶች መካከል አንድ ስድሰተኛ የሚሆን ሲሆን ተምቹ የሚያደርሰው ጥፋት የረሃቡንና የድርቁን ሁኔታ በከፍተኛ ደረጃ ሊያስፋፋው ይችላል ተብሎ ተሰግቷል። ተምቹ በሰዓት ከ 100 ኪሎ ሜትር በላይ የመብረርና በአንድ ጊዜ 1500 እስከ 2000 እንቁላል የመፈልፈል አቅም እንዳለው ባለሙያዎች ይናገራሉ። በወያኔ የእርሻና የተፈጥሮ ሀብት ሚኒስተር ተምቹን ለማጥፋት የተደረገው ጥረት የተወሰነ ውጤት ቢኖረውም ተምቹን ለመቆጣጠር ያልተቻለ በመሆኑ በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ ይገኛል።

የሕወሓት መንግስትን ከድተው በኤርትራ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ኃይልን የተቀላቀሉት ወታደሮች ምስጢር ማውጣት ጀመሩ source zhabesha



የሕወሓት መንግስትን ከድተው በኤርትራ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ኃይልን የተቀላቀሉት ወታደሮች ምስጢር ማውጣት ጀመሩ