Monday, March 20, 2017

Netsanet Le Ethiopia Radio Interview With Professor Ezekiel Gebissa 

Netsanet Le Ethiopia Radio Interview With Professor Ezekiel Gebissa 






Netsanet Le Ethiopia Radio Interview With Professor Ezekiel Gebissa

Friday, March 17, 2017

አምባጊዮርጊስ ላይ ጥቃት ማን ፈፀመ? – አስናቀው አበበ source ሳተናው

 28
ከቦታው በጥንቃቄ ጊዜ ወስደን እንዳጣራነው ጎንደር/ወገራ አውራጃ በአምባጊዮርጊስ ከተማ የፖሊስ ጣቢያ ላይ እሮብ እለት ድንገተኛ ተኩስ ከፍተው የነበሩት የአርበኞች ግንቦት ሰባት ተወርዋሪ ሃይል መሆኑን ለመረዳት ችለናል። ይህ ነው የሚባል ጉዳት መድረሱን ማረጋገጥ ባይቻልም ከሰሞኑ የጎንደር ሆስፒታል በተጎዱ ወታደሮች መጨናነቁን መዘገባችን ይታወቃል።
በሁኔታው የወያኔ ተላላኪ የአካባቢው ባለስልጣናት ክፉኛ መደናገጣቸው ታውቋል። እየተደናበረ ያለው ወያኔ የጎንደር ከተማ ፖሊስ መምሪያ ም/ኮሚሸነርን እና የመምሪያዉ ም/ሀላፊን በተመሳሳይ ወቅት ይዞ ማሰራቸውን መረጃወች ይጠቁማሉ።
አምባጊዮርጊስ ከጎንደር ወደ 40 ኪ.ሜ. ገደማ የምትርቅ ከተማ ስትሆን ወያኔ በቅርብ ጊዜ በጅምላ ህዝብ የፈጀባት ቦታ ናት። አካባቢውን መሰረት ያደረገው የከፋኝ ሃይል ተደጋጋሚ ጀብዱና ድል የፈፀመባት የእንቃሽ አካባቢ መገኛ ናት።
ድል የህዝብ ነው©!

ህዝባችን የሚሻው መሰረታዊ ለውጥን እንጂ ቀጣይ ወታደራዊ አገዛዝንና ባዶ ተስፋን  አይደለም – ሽንጎ source zhabesha

ሕወሀት/ ኢህአዴግ እንደተሽመደመደና መግዛት አንዳቃተው በተዘዋዋሪ አመነ።፤ይህ ሁኔታ ሰፊ የህዝብ መነሳሳትን ይቀስቅሳል ብሎ የፈራው ሕወሀት/ኢህአዴግ ከስድስት ወራት በፊት የጀመረውን ወታደራዊ አገዛዝ በመላ ኢትዮጵያ ይቀጥላል ሲል በጠቅላይ  ሚኒስቴር ሐይለማርም ደሳለኝ በኩል  በዛሬው እለት ለ”ፓርላማ” በቀረበው  ሪፖርት አረጋግጧል። አስቂኝ የሆነው ይህ ንግግር፣ 82% የኢትዮጵያ ህዝብ አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲቀጥል ይፈልጋል ይላል። በአማራና ኦሮሚያ ክልል የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን (65% ኢትዮጵያውያን) ስርአቱን ሙሉ በሙሉ እየተቃወሙት እንደሆነ እየታወቀ 82%  ድጋፍ ከየት እንደሚመጣ የህወሀት/አህአዴግ በለስልጣኖች ብቻ ናቸው የሚያውቁት፡፡ እነርሱ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚሉት የህወሀት/ ኢህአዴግን አባላት ብቻ ከሆነ ሌላ ነገር ነው።
ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ንግግራቸው በተለይ ኢኮኖሚውንና እድገትን በተመለከተ  እጅግ የተምታታና መጨበጫም የሌለው ነው፣ ባንድ  በኩል የኢትዮጵያን  ህዝብ ተጨባጭነት የሌለው “እናድጋለን” የሚል ባዶ  ተስፋ ሊመግቡ የሞከሩ ሲሆን  በሌላ በኩል ግን በተጨባጭ የእርሻ ምርት እንደቀነሰ፣ የውጭ ንግድ ገቢ ለሶስት ተከታታይ አመታት እንዳሽቆለቆለ፣ የዋጋ ግሽበት እንዳሻቀበ ከውጭ የሚገኝ እርዳታ እንደወደቀ፣የግብርና ምርት ኤክስፖርት እንደደቀቀ ፤ ድርቅ በየቦታው እንደተስፋፋ፣የሀገሪቱ እዳ እየጨመረ እንደሆነ ስርአቱ ከ26 አመት ስልጣን በሓላ ሀገሪቱን በምግብ ራሷን ማስቻል እንዳልቻለ አምነዋል። ባጠቃላይ ሚዛን ሲታይ ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ስርአቱን እድገት ሳይሆን ውድቀት አሽመድምዶ እንደያዘው አምነዋል።
የፖለቲካ ድርድርን በሚመለከት የተናገሩትም እንዲሁ እጅግ አሳዛኝ ፤ ሀገራዊ ሀላፊነት የጎደለው  ነው፡ “ማንም አስገድዶን አይደለም ለድርድር የቀረብነው” “ተጽእኖ ሲደረግብን በፍጹም ፍንክች አንልም” በማለት በግልጽ ቋንቋ ይህ መንግስት እጅግ ችክ ያለ ደረቅ አንደሆነ፣ እና ከሁኔታወች ጋር መጓዝ እንደማይችል፣ ለእውነተኛ ለውጥ የተዘጋጀ እንዳልሆነ ሰጥቶ መቀበልን ሳይሆን በራሱ መስመር ብቻ መጓዝን እንደሚገፋ አረጋግጠዋል። የተጀመረው ድርድር እሩቅ እደማይሄድም የጥርጣሬ ጥላ አጥልተውበታል። ይህ ታዲያ ሀላፊነት የጎደለው ለፍጥጫና ለቀጣይ ግጭት የሚጋብዝ እንጂ ለሰላም በር ከፋች አይደለም፡፡
ያው እንደተለመደው አሁንም ፖለቲካዊ ተቃውሞን በወታደራዊ ሀይል ለመጨፍለቅ አስቸኳይ ጊዜ አዋጁን እንደሚያራዝሙ ከመግለጽ ውጭ፤ ጠቅላይ ሚኒስቴሩ በዚህ ንግግራቸው በሀገራችን የተከሰቱትን ዋና ዋና የፖለቲካ ግጭቶች  ለመቅረፍ ምን እንደሚያደርጉ ያቀረቡት ምንም ተጨባጭ የፖለቲካ መፍትሄ የለም።
በራሳቸው ጭንቅ የተወጠሩት ጥቅላይ ሚኒስቴሩና  ንግግራቸው ሁሉ ያተኮረው በድርኢጅታቸው የውስጥ ፡ተሀድሶ” ላይ ነው። ይህ አይነቱ ንግግር ለፓርቲያቸው የውስጥ ስበሰባ እንጂ ለህዝብ የሚቀርብ አይደለም፣፡ ምክንያቱም  ከ 26 አመት ስልጣን በሓላ የኢትዮጵያ ህዝብ ስለ ህወሀት/ኢህአዴግ መታደስ ቅንጣት ያክል ስሜት የለውም። የሚፈልገው ግፈኛውንና ከፋፋዩን የኢህአዴግ /ህወሀትን ስርአት በማስወገድ የስርአት ለውጥን እውን ማድረግ  ነውና።
ባጠቃላይ ሙሉውን ንግግር አንገታቸውን ደፍተው የፈጸሙት  ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ከቃላት ይልቅ በድምጻቸውና  በሰውነታቸው ሁኔታ  (ቦዲ ላንጉጅ) ምን ያክል የተጨነቁና ተስፋም የቆረጡ  አንደሆነ ግልጽ አድርገዋል።
እጅግ ገላጭ የሆነው ሌላው ጉዳይ ደግሞ ተሰባሳቢዎቹ “የፓርላማ ተወካዮች”  ግማሾቹ ሲያንቀላፉ የታዩ ሲሆን ሌሎቹ ደግሞ “ምን ማለቱ ነው” የሚል በሚመስል ሁኔታ እርስ በርስ ሲንሾካሾኩ ተስተውሏል።
ከዚህ ውጭ ግን የሚገርመው በሙሉ ንግግሩ መሀል የተለመደው ረጂም ተከታታይ ጭብጨባ እንኳ አለመደመጡ ጠቅላላ ታዳሚዎቹ ምን ያክል በጭንቅ ላይ እንደሆኑ አሳብቆባቸዋል።
አዎ ስርአቱ የሚገኝበት ሁኔታ በውነትም የሚያሰጨንቅ ነው። የእርሻ ምርት  ከወደቀ፣ ኑሮ ውድነት ከጨመረ፣ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት ካልተቻለ፣ የውጭ እርዳታ ከቀነሰ፣ ድርቅ ከተስፋፋ ፣ ኮንትሮባንድ ንግድ ሀገሪቱን ካጥለቀለቀ፤ ምርታቸውን የሚገዛ እየቀነሰ ከሄደ   የፖለቲካ ግጭቱ ከቀጠለ ህዝቡ ስቃዩ ይጨምራል ማለት  ነው፤ ህዝብ ይራባል  ማለት ነው ። ህዝብ የመብት ማጣቱ ይጨምራል ማለት ነው። ታዲያ ባለፈው አመት በኢትዮጵያ እንዲሁም  ከጥቂት አመታት በፊት  በግብጽ ሊቢያና የመን እንዳየነው፤ የተከፋ ህዝብ፣ የተራበ ህዝብ መሪዎቹን ይበላል። ይህ ማንም የማይገታው የተፈጥሮ ህግ ነው።
እኛ የምንለው  መፍትሄው መቆዘምና መጨነቅ ወይም እውነታውን መካድ፣ በጨለማ ውስጥ መደናበርና  ባዶ ተስፋ ለመመገብ መሞከር ሳይሆን ሀገራችንንና ህዝባችንን ገደል እየጨመረ ያለውን የህወሀት/ኢህአዴግ ፖሊሲ አሽቀንጥሮ መጣል ነው። በሙሉ ቅንነት ለሁሉም የሚጠቅመውን ሁሉን አቀፍ የሆነ ብሄራዊ መግባባት እና ብሄራዊ እርቅን ተግባራዊ አሁኑኑ ማድረግ ነው።
ለዚህም
  • በተለያየ ሰበብ አስባብ  ለእስር የተዳረጉትን የፖለቲካ እስረኞች ሁሉ በተለይም ደግሞ አንደ አንዱአለም አራጌ፣ በቀለ ገርባ፤ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲናና ኮሎኔል ደመቀን የመሳሰሉ የፖለቲካ መሪዎች፣ እንደ እስክንድር ነጋና ተመስገን ደሳለኝ፣ የመሳሰሉት ጋዜጠኞች  ወዘተ አሁኑኑ እንዲፈቱ  ማድረግ እጅግ አስፈላጊ ይሆናል። ባጠቃላይ የህሊናና የፖለቲካ እሥረኞች ሁሉ አላንዳች ቅድመ ሁኔታ  ከእሥር ነጻ ሊሆኑ ይገባል።
  • መሰረታዊ የሆኑ የዴሞክራሲ መታፈንን፣ የሰብአዊ መብት መገፈፍን፣ የህግ የበላይነት መጥፋትን የመሰሉት ጉዳዮች በግልጽ ውይይት ተደርጎባቸው እነዚህን እውነታዎች ለ26 አመታት ያስቀጠለው ሁኔታ የሚወገድበትን መንገድ በጋራ መሻት የግድ ይላል፡። በግፍ የተጎዱ ሁሉ ሊካሱ የሚችሉበትን ሁኔታም ማመቻቸት ተገቢ ነው።
  • መሰረታዊ መብትን የሚገድቡና የሚጥሱ ህግጋቶችን ለምሳሌ የሲሺክ ማህበራትን፣ የፖለቲካና  የመብት ታጋይ ድርጅቶችን እንዲሁም መስል  እንቅስቃሴዎችን የሚያኮላሸውን ህግ፣ የጸረ ሽብርተኝነት ህግ፤ የሚዲያ ሕግ ወዘተ መሰረዝ አስፈላጊ ነው። ህገ መንግስቱም የሀገራችንን ህዝብ ፍላጎት በሚያንጸባርቅ መልኩ የሚሻሻልበትን ሁኔታ መመርመርና መተግበር ይኖርበታል።
  • በቅርቡ በአማራ በኦሮሞና ሌሎችም ክልሎች የተነሱትን የብዙ ወገኖቻችን ህይወት የተገበረባቸው መሰረታዊ የህዝብ ጥያቄዎች በጥሞናና በሀገራዊ ሀላፊነት መመርመር መወያየትና መፍትሄ መፈለግን የግድ ይላል፡ በነዚህ አካባቢዎች የሚካሄደውን ወታደራዊ ዘመቻም ባሰቸኳይ መስቆም የግድ ነው፡
  • በህዝባችን ላይ የተጫነውን የጭንቅ ቀንበር ማስወገድ አስፈላጊ ነው። ለዚህም በመላ ሀገሪቱ የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እና ኮማንድ ፖስት ባሰቸኳይ ማንሳት ያስፈልጋል። ማንም ኢትዮጵያዊ  አሁንም ከየሰፈሩ እየተጎተተ የማይታሰር በወታደርና ደህንነት ሰራተኞች የማይደበደብ፣ እንደፈለጉ የማያስሩት እንደሚሆን ከቃላት ባለፈ በተጨባጭ ማሳየት አስፈላጊም አጣዳፊም ሆኖ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር መሆን አለበት።
  • በሀገሪቱ መሰረታዊ የፍትህ ሥርአት፣ የምርጫ ቦርድ፣ የምርጫ ሂደት፣ የሰራዊት እዝ፤ የደህንነት ቢሮ፤ ወዘተ ከፖለቲካዊ ወገንተኝነትና የፓርቲ ተቀጽላነት ወጥተው መላ ህዝብን ሊያገለግሉ በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ውይይት ማካሄድና መሰረታዊ የእርምት እርምጃም መወሰድ ይኖርበታል።
  • የጋራ ችግሮቻችንን ከስር መሰረቱ ለመፍታትና ብሄራዊ መግባባትና እርቅ ውጤታማ እንዲሆን ከተፈለገ፣ አግላይነትን አስወግዶ በሀገር ጉዳይ ያገባኛል የሚሉ ሁሉ የሚሳተፉበት ሂደትን ተግባራዊ ማድረግ የግድ ይላል። ብሄራዊ መግባባትና እርቅ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ፣ ስብስብ ወይም ድርጅት የፈለገውን ወስኖ በሌላው ላይ የሚጭነው ወይም “ከፈለጋችሁ ተቀበሉ ካልፈለጋችሁ ተውት “ የሚባል ሳይሆን፣ ሁሉም ወገን የሂደቱም ሆነ የውጤቱ ባለቤት ሊሆኑ የሚችሉበት መሆን ይኖርበታል። ያሁኑ አካሄድም ገና ከጅምሩ ሁሉንም ባለድርሻዎች ያሳተፈ እንዲሆን ማድረግ ያስፈልጋል።
ሽንጎ ደግሞ ደጋግሞ እንደገለጸው ፍላጎታችን በሀገራችን ውስጥ ህገ መንግስታዊ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን እውን ማድረግ እንዲሁም አንድነት፣ እኩልነት፣ የህግ የበላይነትና ዴሞክራሲያዊ መብትን ተግባራዊ ማድረግ ሲሆን፣ ይህን በማድረግም የአመጽ፣ የጦርነት፣ የአሳሪና ታሳሪ አዙሪት፣ ቂም በቀልና ቁርሾ  እንዲያከትም ማድረግ ነው።
በ26 አመት ተሞክሮ እንደማይሰራ የተረጋጋጠን አካሄድ ለማስቀጠል መሞከር ትርፉ ይበልጥ ግጭትንና ሁከትን መጋበዝ ብቻ ነው።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

Thursday, March 16, 2017

ውክልናቸውን በግላቸው ያፀደቁ የብሄር ፖለቲከኞች – ዳንኤል ሃይሌ

ሁሉም ሊባል በሚችል መልኩ በብሄር ተደራጂተናል የሚሉት ድርጅቶች ገና ከስልጣን ደጃፍ ሳይደርሱ ድፍረታቸው እና ንቀታቸው ማንነታቸውን ፍንትው አርጎ እያሳየነው።
ዛሬ ማውራት የምፈልገው እኔ ስለወጣሁበት አማራ ነው የሌሎቹን በይደር እንያዘው። የአማራን ህዝብ መደራጀት ከቶ ማንም የሚቃወም ይኖራል ብዬ አላስብም ምክንያቱም ስለዲሞክራሲ የምናልም ከሆነ ሰዎች በምንም ይሁን በምንም የመደራጀት መብታቸውን ልናከብር ይገባል እንዲሁም እነሱም የሌላውን የማክበር ግዴታ አለባቸው ብለን እናምናለን። ፍትህ እና ዲሞክራሲ በጠፍባት ሀገር ዜጎች በማንኛውም መልኩ የመደራጀትና ሀሳባቸውን በነፃነት ገልፀው መኖር በማይቻልበት ሁኔታ ውስጥ ሆነን እኮ በምን ስሌት ነው እኔ የዚህ ቢሄር ተወካይ ነኝ ወይም በግልፅ ቋንቋ “እኔ የአማራ ብሄር ተወካይ ነኝ እደራደርለታለሁ” የምንለው?
አዎ እውነት ነው የአማራ ህዝብ የሞት አዋጅ የታወጀበት ባልሰራው በደል ባለፋት 25 ዕመታት የዘር ማጥፍት ሲፈፅምበት ቆይቷል። ለዛም ነው ተደራጅቶ እራሱን መታደግ አለበት የምንለው ሆኖም ባሳለፍነው አንድ አመት ውስጥ የተፈለፈሉት ታላቁን የአማራ ህዝብ እንወክላለን የሚሉን ድርጅቶች ህዝባችን ብለው የተነሱለትን ህዝብ ስነልቦና እንኳን ማንበብ የማይችሉ ከራሳቸውም የተጣሉ ሆነው አግኝተናቸዋል። አብዛኛዎቹ የተፈበረኩት በወያኔ የውጭ የፓለቲካ እስትራቴጂክ መዋቅር ውስጥ መሆኑን በግዜ ተጉዘን መረዳት ችለናል ፤ እደውም አንዳንዴም “አግ7 ወደስልጣን ከሚመጣ ከብአዴን ጋር ተስማምተን እንሰራለን” ትዕግስታቸው ሲያልቅ ብለው የሚናገሩም አሉ። ምን እሚሉት ፈሊጥ ነው ከገዳይ ጋር እሰራለሁ ማለት?
የህዝብ ውክልና ምንድነው?
ኢትዮጵያ አሁን ባለችበት የፓለትካ አጣብቂኝ ውስጥ ሆነን ስለህዝብ ውክልና ማውራት ማለት አላዋቂነት ነው ተብሎ ሊታለፍ አይገባም በማንአለብኝነት የተሞላ የስልጣን ጥማት የነገሰበት አስተሳሰብ ነው።
አምባገነኑን የወያኔ አፓርታይድ ስርአት ሳንጥል እና በነፃነት አገራችን የፖለቲካ ሜዳ ላይ ፖሊሲያችንን አቅርበን ቆሜልሀለው የምንልውን ህዝብ ይሁኝታ ሳናገኝ አይ እኔ የተወለድኩት ጎጃም፣ጎንደር፣ወሎ…ወዘተ ስለሆነ እኔነኝ ተወካይህ በማንነትህ ላይ እደራደራለሁ ማለት የጠገበውን ወያኔን አዉርዶ የራበውን ምትኩን ማንገስ ነው የሚሆነው። ለዛም ነው ምንም እንኳን የአስተሳሰብ ልዩነት ቢኖረንም አምባገነኑን የወያኔን ስርአት በጋራ ጥለን በነፃነት ለተጨቆነው ህዝብ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ሀሳባችንን አቅርበን ውክልናን የምንረከበው። በተቃራኒው ግን አሜሪካ አገር ቁጭ ብሎ አገር ቤት ወያኔ ሲወድቅ ስልጣን እንደሚያገኝ እርግጠኛ መሆን የሚፈልጉ ቆሜለታለው የሚሉት ወገን ሞት ምንም የማይመስላቸው ሆነው አግኝተናቸዋል።
አግ7 እንኳን እግር በሌላቸው የወያኔ ድርጅቾች በወያኔም አይፈርስ! አግ7 ውስጥ ምንያህል አማሮች እንዳለን እናንተም ታውቃላችሁ አሁን እናንተም ደረታችሁን ነፍታችሁ እየታገልን ነው የምትሉት ትግል ወልዶ ያሳደገው አሁን ላለንበት ያንገዛም እቢተኝነ ማዕበል ያበቃው አግ7 ነው! እኛም አማራ ነን የህዝባችን ሞት የሚገለን።
አልመሸም ገና ብዙ መንገድ ይቀረናል አብረን ብንጟዝ ቶሎ ያሰብንበት እንድርሳለን የወገኑ ስቃይ የሚያመው ሁሉ ልዩነቱን አቻችሎ ለአንድ ጠላት ወያኔ በጋራ ይነሳ!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ዳንኤል ሃይሌ

ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ ከተከዜ በታች ያለ ኢትዮጵያዊ ያላለቀሰበት ጊዜ የለም፤ በአንጻሩ ከተከዜ በላይ ያሉ ዜጎች ዘመናቸው ሁሉ የፍስሃ ሆነ source zhebesha


ከሙሉቀን ተስፋው
ለቀስተኛው፤ ከተከዜ በታች ያለ ሕዝብ:
ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ ከተከዜ በታች ያለ ኢትዮጵያዊ ያላለቀሰበት ጊዜ የለም፤ በአንጻሩ ከተከዜ በላይ ያሉ ዜጎች ዘመናቸው ሁሉ የፍስሃ ሆነ፡፡
እስኪ ትንሾቹን እንይ፤
 ከ1983-86 ዓ.ም በሐረርጌ እስከ 20 ሺህ የሚደርስ ዐማራ በአንድ ዓመት ሲታረድ፣ አጥንታቸው ወደ ወንዝ ሲወረወር፣ አብያተ ክርስቲያናት ሲወድሙ ከተከዜ በላይ ዳንኪራ ይረገጥ ነበር፡፡ በምስራቅ አርሲ የአምስት ወረዳ ዐማራ ቤትና ንብረት ተቃጥሎ ከነነፍሳቸው ወደ ገደል ሲጣሉ፤ በዘንጋዳ ጉድጓድ በጅምላ ሲቀበሩ እየየ ብለን አልቀሰናል፡፡ ወላድ እናቶች ልጃቸው በሳንጃ ከሆዳቸው ላይ የወጣበት ጊዜ በዚሁ በወያኔ ዘመን ነው፡፡ የማይሞላ ገደል ውስጥ የተጨመሩት ዐማሮች፣ ዐይናቸው ተጨፍኖ ወደ ገደል የተወረወሩት መነኮሳትን ማናችንም አልረሳንም፡፡ የመተከልና የወለጋ ጫካዎች በዐማራ አስከሬኖች ሲሞሉ የገዥው ቡድን ዘመዶች አስረሽ ምቺው እያሉ ነበር፡፡
 ከ1972 ዓ.ም ጀምሮ የወልቃይት ዐማራ እናቶች ስለልጆቻቸውና ባሎቻቸው ያላዘኑበት ጊዜ የለም፤ በዚህ ጊዜ ከወንዝ ወዲያ ማዶ ያሉ ሰዎች ምን ይሉ እንደነበር ማንም መገመት አያቅተውም፡፡
 በ1998 ዓ.ም የኮፈሌና የቆሬ ወረዳ ዐማሮች ቤት ንብረታቸው በጨለማ ነዶ ከቀያቸው ሲፈናቀሉ ማንም ምንም ያለ የለም፡፡

 በ1992/3 ዓም በወለጋ የተለያዩ አካባቢዎች ከአንድ ሺህ በላይ ዐማሮች ቤት እየተዘጋባቸው ሲቃጠሉ ሕጻናት ከታዘሉበት እናታቸው ጀርባ እየተቀሙ ወደ ሚነደው እቶን ሲጣሉ መከላከያ ሠራዊት የሚያመልጡትን ዐማሮች በጀርባ ሆኖ ይጨርስ ነበር፡፡ 14000 (ዐሥራ አራት ሺህ) ዐማሮች ተፈናቅለው ቡሬ ላይ ሲቀመጡ የእለት ጉርስ እንኳ የሰጣቸው የመንግሥት አካል አልነበረም፡፡ ጃዊ ላይ ከ800 በላይ በወባ ሲያልቁ የወባ መድኃኒት ያቀረበ የጤና ባለሙያ እንኳ አልነበረም፡፡

 በ1990ዎቹ መጀመሪያ በወያኔና በሻቢያ ጦርነት ከ70 ሺህ በላይ ወንድሞቻችን በጦር በጦርነት ተማግደው አልቀዋል፡፡
 በ1999 ዓ.ም በጂማ ከነቤተክርሲያናቸው ዐማሮች ቤት ተዘግቶባቸው ሲነዱ ማንም ምንም አላለም፡፡
 በ2004-7 በቤንች ማጂ፣ በከማሽ፣ በመተከል፣ ከ32000 በላይ ዐማሮች ቤት ንብረታቸው ወድሞ ሲባረሩ ከተከዜ ማዶ ያሉ ሰዎች ደን ጨፍጫፊ ትምከተኞች ናቸው በማለት ነበር የተሳለቁት፡፡
 በ2007 ዓ.ም በመተከል በአንድ ቀን ሌሊት 160 በላይ ዐማሮች ታርደው ሲያደሩ የተባለ ነገር የለም፤
 በ2007 ዓ.ም በጎንደር ማረሚያ ቤት ከ70 በላይ ሰዎች በእሳት ሲቃጠሉ ምን ተባለ! ምንም፡፡
 በ2008/9 ከ300 በላይ ዐማሮች በጎንደርና በጎጃም በጥይት ተደፍተዋል፤ ገዥው ቡድን ምን አለ! ምንም፡፡
 በደብረዘይት በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ተጠቅጥቀው ሲሞቱ እንኳ ከተከዜ ማዶ አሸንዳ ሲጨፈር ነበር፡፡
ምኑን ተናግረን ምኑን መተው እንችላለን? ከተከዜ በታች ያለን ዜጎች ኑሮ እንዲህ ነው፡፡ በእኛ ላይ ይህ ሁሉ ሲሆን ከተከዜ ማዶ ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ምን መቅሰፍት ደርሶ ይሆን ብየ አሰብኩ፤ ምንም!
ደግነቱ ጊዜ ፈራጅ ነው፤ የሚያለቅሱ የሚስቁበት ጊዜ የሚስቁም የሚያለቅሱበት ዘመን ብዙ ሩቅ አይደለም፡፡

አቶ ለገሰ ወልደሃና እና አንድ የደብረ ብርሃን ባለሀብት ታሰሩ by: Zehabesha


 





ከሙሉቀን ተስፋው
በአቶ ማሙሸት አማረ የሚመራው የመኢአድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለገሰ ወልደሃና መጋቢት 6 ቀን 2009 ዓም ከቤቱ በደኅንነት ታፍኖ ተወስዷል። በደብረ ብርሃን ከተማ ጠባሴ አካባባቢ የፍቅረ ሰላም ሆቴል ባለቤት የሆኑ ባለሀብት ባካባቢው በመገኘታቸው አብረው ታስረዋል። በደኅንነቶችና በፖሊስ አባላት ድብደባ እንደደረሰባቸው ታዛቢዎች የገለጹ ሲሆን ወደ ማዕከላዊ መዛወራቸውን ዛሬ ለማወቅ ችለናል።
አቶ ለገሰ ወ/ሃና ከፓርቲ ሥራው በተጨማሪ የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሀሳብ በመሰንዘርና መረጃ በማድረስ የታወቀ ነው። በተለይ በሸዋ አካባቢ ያለውን የዐማራ ተጋድሎ ለሕዝብ ሳያሳልስ የሚያቀርብ ታታሪ ፖለቲከኛ ነው።

የአርበኞች ግንቦት 7 ታጣቂዎች በሰሜን ጎንደር ዞን የተለያዩ ስፍራዎች ማክሰኞ ምሽት ጥቃት ፈጸምሁ አለ

ከአይን ምስክሮችና ከንቅናቄው ምንጮች ለመረዳት እንደተቻለው በጭልጋ፣ ደንቢያና በጎንደር ዙሪያ ወረዳዎች በተመሳሳይ ቀንና በተቀራራቢ ሰዓት በመንግስት ሃይሎችና ተቋማት ላይ ጥቃት ተፈጽሟል።

በትግል ላይ እያሉ መስዋዕትነት በከፈሉት ሻለቃ መሳፍን ጥጋቡ ወይንም ገብርዬ እንዲሁም በታጋይ ጎቤ መልኬ እና በአበራ ጎባው ስም የተሰየሙት ወታደራዊ ዘመቻዎች፣ ማክሰኞ መጋቢት 5 ፥ 2009 የመከላከያ ሰራዊት አባላትን መግደልና መቁሰል ጭምር ማስከተላቸውንም ለመረዳት ተችሏል።
ዘመቻ “ዋዋ” የሚል ስያሜ በተሰጠው በዚሁ ጥቃት ከጎንደር 80 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው በመከላከያ ሰራዊት ካምፕ ላይ ጥቃት ተሰንዝሯል። በጭልጋ ወረዳ ነጋዴ ባህር ከተማ በሰፈረው የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ በተሰነዘረ ድንገተኛ ጥቃት 3 ወታደሮች ሲገደሉ፣ 15 መቁሰላቸው ተመልክቷል። በአምስቱ ላይ የደርሰው ጉዳት ከፍተኛ በመሆኑ ጎንደር ሬፈራል ሆስፒታል ሲወስዱ፣ ቀላል ጉዳት የደርሰባቸው 7 ወታደሮች በመተማ ገንዳ ውሃ ሆስፒታል በህክምና ላይ መሆናቸውን የተገኘው ዜና ያስረዳል።
በቅርቡ በትግል ሜዳ ላይ እያሉ የተሰውትን ጎቤ መልኬን ለማስታወስም በስማቸው መጠሪያ “ዋዋ” የተሰየመው ዘመቻ ተሳታፊ የሆኑት የአርበኞች ግንቦት 7 ተዋጊዎች ጥቃቱን ፈጽመው ወደ ነበሩበት መመለሳቸው የተገለጸ ሲሆን፣ በመከላከያ ሰራዊት በኩል በቡድን መሳሪያ የተደገፈ የአጻፋ ምላሽ መሰጠቱም ተመልክቷል። በመትረየና ላውንቸር የተደገፈውን የአጸፋ ምላሽ ተከትሎ በአካባቢው ውጥረት መንገሱንና የትራንስፖርት አገልግሎት መቋረጡም ተመልክቷል።
በዚሁ በጎንደር ዞን ደንቢያ ወረዳ በተመሳሳይ ቀን ዘመቻ ገብርዬ በሚል በተሰየመው ወታደራዊ ዘመቻ በቆላ ድባ ከተማ በሚገኝ የከተማው አስተዳደር ጽ/ቤት ላይ በተከፈተ ዘመቻ የአስተዳደር ጽ/ቤቱ በከፊል ሲወድም፣ የአስተዳዳሪው መኪና መቃጠሉንም የመጣው ዜና ያስረዳል። በተመሳሳይ ጯሂት ከተማ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በካምፕነት በሚጠቀሙበት ቁጥር 2 በተባለው ጽ/ቤት ላይ በተሰነዘረ ጥቃት በወታደሮቹ ላይ የቃጠሎ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
በአብራጅራ ከተማ አብራጅ ጽ/ቤት በሰፈሩ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ እንዲሁም በቸንከር ቀበሌ የከተማዋ ኮማንድ ፖስት ማዘዣ ላይ ጥቃት ተፈጽሟል። በጥቃቱ የቸንከር ቀበሌ ኮማንድ ፖስት ማዘዣ ጣቢያ ሲወድም፣ አንድ የኮማንድ ፖስቱ አባል መጎዳቱንና አንድ መጋዘን መቃጠሉን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።
በሰሜን ጎንደር አካባቢዎች መሳሪያ አንስተው በትግል ላይ ከነበሩት አንዱ በነበረውና መስዋዕትነት በከፈለው በአበራ ጎባው ስም በተመሳሳይ ቀን በጎንደር ዙሪያ የአርበኞች ግንቦት 7 ሃይሎች ጥቃት መፈጸማቸውም ተመልክቷል።
የአርበኞች ግንቦት 7 ተዋጊዎች ማክሰኞ መጋቢት 5 ፥ 2009 እኩለ ሌሊት አካባቢ በጎንደር ዙሪያ ወረዳ በደጋማ ከተማ በወህኒ ቤት እንዲሁም ኮማንድ ፖስቱ በሚጠቀምባቸው ቢሮዎች ላይ ጥቃት መፈጸሙ ታውቋል። እንዲሁም የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል በሆኑት በአቶ ደሴ ዘገየ መኖሪያ ቤት ላይም ተመሳሳይ ጥቃት መከተሉንም የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።