Thursday, March 16, 2017

ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ ከተከዜ በታች ያለ ኢትዮጵያዊ ያላለቀሰበት ጊዜ የለም፤ በአንጻሩ ከተከዜ በላይ ያሉ ዜጎች ዘመናቸው ሁሉ የፍስሃ ሆነ source zhebesha


ከሙሉቀን ተስፋው
ለቀስተኛው፤ ከተከዜ በታች ያለ ሕዝብ:
ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ ከተከዜ በታች ያለ ኢትዮጵያዊ ያላለቀሰበት ጊዜ የለም፤ በአንጻሩ ከተከዜ በላይ ያሉ ዜጎች ዘመናቸው ሁሉ የፍስሃ ሆነ፡፡
እስኪ ትንሾቹን እንይ፤
 ከ1983-86 ዓ.ም በሐረርጌ እስከ 20 ሺህ የሚደርስ ዐማራ በአንድ ዓመት ሲታረድ፣ አጥንታቸው ወደ ወንዝ ሲወረወር፣ አብያተ ክርስቲያናት ሲወድሙ ከተከዜ በላይ ዳንኪራ ይረገጥ ነበር፡፡ በምስራቅ አርሲ የአምስት ወረዳ ዐማራ ቤትና ንብረት ተቃጥሎ ከነነፍሳቸው ወደ ገደል ሲጣሉ፤ በዘንጋዳ ጉድጓድ በጅምላ ሲቀበሩ እየየ ብለን አልቀሰናል፡፡ ወላድ እናቶች ልጃቸው በሳንጃ ከሆዳቸው ላይ የወጣበት ጊዜ በዚሁ በወያኔ ዘመን ነው፡፡ የማይሞላ ገደል ውስጥ የተጨመሩት ዐማሮች፣ ዐይናቸው ተጨፍኖ ወደ ገደል የተወረወሩት መነኮሳትን ማናችንም አልረሳንም፡፡ የመተከልና የወለጋ ጫካዎች በዐማራ አስከሬኖች ሲሞሉ የገዥው ቡድን ዘመዶች አስረሽ ምቺው እያሉ ነበር፡፡
 ከ1972 ዓ.ም ጀምሮ የወልቃይት ዐማራ እናቶች ስለልጆቻቸውና ባሎቻቸው ያላዘኑበት ጊዜ የለም፤ በዚህ ጊዜ ከወንዝ ወዲያ ማዶ ያሉ ሰዎች ምን ይሉ እንደነበር ማንም መገመት አያቅተውም፡፡
 በ1998 ዓ.ም የኮፈሌና የቆሬ ወረዳ ዐማሮች ቤት ንብረታቸው በጨለማ ነዶ ከቀያቸው ሲፈናቀሉ ማንም ምንም ያለ የለም፡፡

 በ1992/3 ዓም በወለጋ የተለያዩ አካባቢዎች ከአንድ ሺህ በላይ ዐማሮች ቤት እየተዘጋባቸው ሲቃጠሉ ሕጻናት ከታዘሉበት እናታቸው ጀርባ እየተቀሙ ወደ ሚነደው እቶን ሲጣሉ መከላከያ ሠራዊት የሚያመልጡትን ዐማሮች በጀርባ ሆኖ ይጨርስ ነበር፡፡ 14000 (ዐሥራ አራት ሺህ) ዐማሮች ተፈናቅለው ቡሬ ላይ ሲቀመጡ የእለት ጉርስ እንኳ የሰጣቸው የመንግሥት አካል አልነበረም፡፡ ጃዊ ላይ ከ800 በላይ በወባ ሲያልቁ የወባ መድኃኒት ያቀረበ የጤና ባለሙያ እንኳ አልነበረም፡፡

 በ1990ዎቹ መጀመሪያ በወያኔና በሻቢያ ጦርነት ከ70 ሺህ በላይ ወንድሞቻችን በጦር በጦርነት ተማግደው አልቀዋል፡፡
 በ1999 ዓ.ም በጂማ ከነቤተክርሲያናቸው ዐማሮች ቤት ተዘግቶባቸው ሲነዱ ማንም ምንም አላለም፡፡
 በ2004-7 በቤንች ማጂ፣ በከማሽ፣ በመተከል፣ ከ32000 በላይ ዐማሮች ቤት ንብረታቸው ወድሞ ሲባረሩ ከተከዜ ማዶ ያሉ ሰዎች ደን ጨፍጫፊ ትምከተኞች ናቸው በማለት ነበር የተሳለቁት፡፡
 በ2007 ዓ.ም በመተከል በአንድ ቀን ሌሊት 160 በላይ ዐማሮች ታርደው ሲያደሩ የተባለ ነገር የለም፤
 በ2007 ዓ.ም በጎንደር ማረሚያ ቤት ከ70 በላይ ሰዎች በእሳት ሲቃጠሉ ምን ተባለ! ምንም፡፡
 በ2008/9 ከ300 በላይ ዐማሮች በጎንደርና በጎጃም በጥይት ተደፍተዋል፤ ገዥው ቡድን ምን አለ! ምንም፡፡
 በደብረዘይት በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ተጠቅጥቀው ሲሞቱ እንኳ ከተከዜ ማዶ አሸንዳ ሲጨፈር ነበር፡፡
ምኑን ተናግረን ምኑን መተው እንችላለን? ከተከዜ በታች ያለን ዜጎች ኑሮ እንዲህ ነው፡፡ በእኛ ላይ ይህ ሁሉ ሲሆን ከተከዜ ማዶ ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ምን መቅሰፍት ደርሶ ይሆን ብየ አሰብኩ፤ ምንም!
ደግነቱ ጊዜ ፈራጅ ነው፤ የሚያለቅሱ የሚስቁበት ጊዜ የሚስቁም የሚያለቅሱበት ዘመን ብዙ ሩቅ አይደለም፡፡

አቶ ለገሰ ወልደሃና እና አንድ የደብረ ብርሃን ባለሀብት ታሰሩ by: Zehabesha


 





ከሙሉቀን ተስፋው
በአቶ ማሙሸት አማረ የሚመራው የመኢአድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለገሰ ወልደሃና መጋቢት 6 ቀን 2009 ዓም ከቤቱ በደኅንነት ታፍኖ ተወስዷል። በደብረ ብርሃን ከተማ ጠባሴ አካባባቢ የፍቅረ ሰላም ሆቴል ባለቤት የሆኑ ባለሀብት ባካባቢው በመገኘታቸው አብረው ታስረዋል። በደኅንነቶችና በፖሊስ አባላት ድብደባ እንደደረሰባቸው ታዛቢዎች የገለጹ ሲሆን ወደ ማዕከላዊ መዛወራቸውን ዛሬ ለማወቅ ችለናል።
አቶ ለገሰ ወ/ሃና ከፓርቲ ሥራው በተጨማሪ የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሀሳብ በመሰንዘርና መረጃ በማድረስ የታወቀ ነው። በተለይ በሸዋ አካባቢ ያለውን የዐማራ ተጋድሎ ለሕዝብ ሳያሳልስ የሚያቀርብ ታታሪ ፖለቲከኛ ነው።

የአርበኞች ግንቦት 7 ታጣቂዎች በሰሜን ጎንደር ዞን የተለያዩ ስፍራዎች ማክሰኞ ምሽት ጥቃት ፈጸምሁ አለ

ከአይን ምስክሮችና ከንቅናቄው ምንጮች ለመረዳት እንደተቻለው በጭልጋ፣ ደንቢያና በጎንደር ዙሪያ ወረዳዎች በተመሳሳይ ቀንና በተቀራራቢ ሰዓት በመንግስት ሃይሎችና ተቋማት ላይ ጥቃት ተፈጽሟል።

በትግል ላይ እያሉ መስዋዕትነት በከፈሉት ሻለቃ መሳፍን ጥጋቡ ወይንም ገብርዬ እንዲሁም በታጋይ ጎቤ መልኬ እና በአበራ ጎባው ስም የተሰየሙት ወታደራዊ ዘመቻዎች፣ ማክሰኞ መጋቢት 5 ፥ 2009 የመከላከያ ሰራዊት አባላትን መግደልና መቁሰል ጭምር ማስከተላቸውንም ለመረዳት ተችሏል።
ዘመቻ “ዋዋ” የሚል ስያሜ በተሰጠው በዚሁ ጥቃት ከጎንደር 80 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው በመከላከያ ሰራዊት ካምፕ ላይ ጥቃት ተሰንዝሯል። በጭልጋ ወረዳ ነጋዴ ባህር ከተማ በሰፈረው የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ በተሰነዘረ ድንገተኛ ጥቃት 3 ወታደሮች ሲገደሉ፣ 15 መቁሰላቸው ተመልክቷል። በአምስቱ ላይ የደርሰው ጉዳት ከፍተኛ በመሆኑ ጎንደር ሬፈራል ሆስፒታል ሲወስዱ፣ ቀላል ጉዳት የደርሰባቸው 7 ወታደሮች በመተማ ገንዳ ውሃ ሆስፒታል በህክምና ላይ መሆናቸውን የተገኘው ዜና ያስረዳል።
በቅርቡ በትግል ሜዳ ላይ እያሉ የተሰውትን ጎቤ መልኬን ለማስታወስም በስማቸው መጠሪያ “ዋዋ” የተሰየመው ዘመቻ ተሳታፊ የሆኑት የአርበኞች ግንቦት 7 ተዋጊዎች ጥቃቱን ፈጽመው ወደ ነበሩበት መመለሳቸው የተገለጸ ሲሆን፣ በመከላከያ ሰራዊት በኩል በቡድን መሳሪያ የተደገፈ የአጻፋ ምላሽ መሰጠቱም ተመልክቷል። በመትረየና ላውንቸር የተደገፈውን የአጸፋ ምላሽ ተከትሎ በአካባቢው ውጥረት መንገሱንና የትራንስፖርት አገልግሎት መቋረጡም ተመልክቷል።
በዚሁ በጎንደር ዞን ደንቢያ ወረዳ በተመሳሳይ ቀን ዘመቻ ገብርዬ በሚል በተሰየመው ወታደራዊ ዘመቻ በቆላ ድባ ከተማ በሚገኝ የከተማው አስተዳደር ጽ/ቤት ላይ በተከፈተ ዘመቻ የአስተዳደር ጽ/ቤቱ በከፊል ሲወድም፣ የአስተዳዳሪው መኪና መቃጠሉንም የመጣው ዜና ያስረዳል። በተመሳሳይ ጯሂት ከተማ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በካምፕነት በሚጠቀሙበት ቁጥር 2 በተባለው ጽ/ቤት ላይ በተሰነዘረ ጥቃት በወታደሮቹ ላይ የቃጠሎ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
በአብራጅራ ከተማ አብራጅ ጽ/ቤት በሰፈሩ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ እንዲሁም በቸንከር ቀበሌ የከተማዋ ኮማንድ ፖስት ማዘዣ ላይ ጥቃት ተፈጽሟል። በጥቃቱ የቸንከር ቀበሌ ኮማንድ ፖስት ማዘዣ ጣቢያ ሲወድም፣ አንድ የኮማንድ ፖስቱ አባል መጎዳቱንና አንድ መጋዘን መቃጠሉን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።
በሰሜን ጎንደር አካባቢዎች መሳሪያ አንስተው በትግል ላይ ከነበሩት አንዱ በነበረውና መስዋዕትነት በከፈለው በአበራ ጎባው ስም በተመሳሳይ ቀን በጎንደር ዙሪያ የአርበኞች ግንቦት 7 ሃይሎች ጥቃት መፈጸማቸውም ተመልክቷል።
የአርበኞች ግንቦት 7 ተዋጊዎች ማክሰኞ መጋቢት 5 ፥ 2009 እኩለ ሌሊት አካባቢ በጎንደር ዙሪያ ወረዳ በደጋማ ከተማ በወህኒ ቤት እንዲሁም ኮማንድ ፖስቱ በሚጠቀምባቸው ቢሮዎች ላይ ጥቃት መፈጸሙ ታውቋል። እንዲሁም የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል በሆኑት በአቶ ደሴ ዘገየ መኖሪያ ቤት ላይም ተመሳሳይ ጥቃት መከተሉንም የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።

Wednesday, March 15, 2017

ለሥልጠና ወደ አድዋ የተወሰዱ የወልቃይት ዐማሮች በድብደባ ጉዳት ደረሰባቸው ከሙሉቀን ተስፋው source zhabesha


ከሙሉቀን ተስፋው
የ10ኛ ክፍል ትምህርታቸውን የጨረሱ የወልቃይት ወጣቶችን አሰልጥኜ ሥራ አስይዛችኋለሁ በማለት ነበር ሕወሓት ወደ አድዋ የወሰዳቸው፡፡ ከወልቃይትና ጠገዴ አካባቢዎች ተመልምለው የተወሰዱ ወጣቶች አድዋ ሲደርሱ ግን የጠበቁትን ሥልጠና አላገኙም፡፡
አብረዋቸው በሚማሩ የትግራይ ተማሪዎችና አስተማሪዎች ‹‹ስለምን ዐማራ ነን አላችሁ፤ ትግሬ የተጠላው በእናንተ ምክንያት ነው!›› የሚል ወከባና ጥያቄ ይደርስባቸዋል፡፡ ከዚያ ወጣቶቹ ‹‹ታዲያ ምን ልንል ነው፤ እኛ እኮ ዐማራ ነን›› የሚል የማያወላዳ ምላሽ ይሰጣሉ፡፡
ትናንት መጋቢት 5 ቀን 2009 ዓ.ም ለሥልጠና የሔዱት ሁሉም ወጣቶች ያለምንም ረዳት በሰው አገር የተደበደቡ ሲሆን ሐጂ የተባለ ወጣት ከፍተኛ የአከርካሪ ጉዳት ደርሶበታል ተብሏል፡፡ በድብደባው ጉዳት የደረሰባቸው ዐማሮች እስካሁን ምንም ዓይነት ሕክምና ካለማግኘታቸውም በተጨማሪ ወደ ወልቃይት እንዳይመለሱ ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገባቸው ነው ተብሏል፡፡ ወደ ወልቃይት ከተመለሱ ለበለጠ አደጋ እንደሚጋለጡና እንደሚታሰሩም ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡

ኖርን እና ሞትን! Posted by: Zehabesh 

ኖርን እና ሞትን!










Tuesday, March 14, 2017

መንግስታዊ ቸልተኝነት እና ብሔራዊ የሐዘን ቀን! – (ይድነቃቸው ከበደ) source zhabesha


መንግስት በደረሰበት ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዲሁም ፣ በማህበራዊ ድረ ገጾች በተለያየ መንገድ ይደረግ የነበረው ቅስቀሳ ባሳደረው ግፊት፣ ብሔራዊ የሐዘን ቀን በኢትዮጵያ ሊታወጅ ችሏል።በዚህም መሰረት ፣ ከመጋቢት 3 እስከ መጋቢት 5 ቀን 2009 ዓ.ም ለሦስት ቀን ብሔራዊ የሃዘን ቀን እንዲሆን ተወስኖል።

በመንግስት ግዴለሽነት ምክንያት ብቻ ! በደረሰው የቆሻሻ ክምር መናድ ፣ከ75 ሰው የማያንስ ለሞት የተዳረገ ሲሆን በመቶ የሚቆጠሩ ለከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት ተዳርገዋል ። እንዲሁም ከ250 የማያንሱ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ሲሆን በጊዚያዊ መጠለያ እንዲቆዩ ተደርጓል ። በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የደረሰው አደጋ፣ የዓለማችን ታላላቅ የመገናኛ ብዙሃን በፊት ገጻቸው ሰፊ የዜና ሽፍና ሰጥተውታል ።

መንግስት አደጋው ከደረሰ ከሦስት ቀን በኋላ ፣ በደረሰበት ከፍተኛ ግፊትና ተጽዕኖ ብሔራዊ የሐዘን ቀን ከማወጁ በፊት ፣ በአዲስ አበባ የጀርምን ኢምባሲ በደረሰው አደጋ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን በመግለጽ ፣ በኢምባሲው የጀርመን እና የአውሮፓ ህብረት ባንዲራ ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ በማድረግ ለኢትዮጵያውያን የጀርመን መንግስት አጋርነቱን አሳይቷል ። ዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ተቋማት ፣በደረሰው አደጋ ማዘናቸውን በመግለጽ ፣ ለአደጋው መንስኤ መንግስትን ተጠያቂ አድርጓል ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ፣የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ፣ አደጋው በደረሰበት አካባቢ በመሄድ ፣ የሟች ቤተሰቦችን እያጽናኑ የሚገኝ ሲሆን፣ ከነፍስ አድን ሰራተኞች ጋር በመተባበር ፣ በቆሻሻ ክምር ውስጥ በህይወት የተረፈ እና ጉዳት የደረሰባቸውን በማፈላለግ ላይ ይገኛሉ። አደጋው በተከሰተበት ቦታ የተገኘው የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ወንድም ፣ አቶ ታሪኩ ደሳለኝ (ሚኪ) በቦታው ተገኝቶ በማህበራዊ ድረ ገጹ እንደገለጸው ከሆነ ፣ “ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የሞቱት ነብስ ይማራ ለማለት ቤተሰቦቻቸውን ለማፅናናት ተገኝቻለሁ። በየአምስት ሜትሩ ድንኳን ተተክሎ ማየት ያሰደነግጣል። አንዳንዱ ጋር ለሦስት ለአራተ ሰው በአንድ ድንኳን ሀዘን ተቀምጠዋል። አሁንም ከቆሻሻው ክምር አስክሬን እየወጣ ነው። እኔ ከደረስኩበት ከ12 እስከ 3 ሰዓት ብቻ 12 አስክሬኖች ወጥተዋል። ነዋሪዎቹ እንደሚናገሩት ይሄ ከላይ ያለው ናዳ ቆሻሻ ውስጥ የተገኙ ናቸው ገና የታቸኛወ ውስጥ ይቀራል ብለዋል። አሁንም ውሃ መብራት የለም።አሁንም በዙ ሰው አልወጣም ብዙዎች ያለመጠለያ ቀርተዋል።የተቻላችሁን የሀል ድግፍ እንድታደርግ “በማለት የተሰማውን ገልጸዋል ።

ሌላው የዓይን እማኝ የሆነው ጋዜጠኛ ጌጡ ተመስገን ፣ በትላንትናው ዕለት በተካሄደው የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተገኝቶ ሃሳብን እንደሚከተለው ገልጸዋል ።”50ዎቹ በደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል ። የሟቾቹ ቁጥር 65
ደርሷል። ፍለጋው እንደቀጠለ ነው። ከሟቾቹ ውስጥ የአንድ ቤት አምስት የቤተሰብ አባላት ይገኙበታል ። ኮልፌ እስላም መቃብር ሀዘንተኛው ነስሩ ሁሴን ተጠጋሁት፣ “እህቴን፣ የእህቴ ሁለት ልጆች፣ የወንድሜ ሚስት ከነልጇ ይሄው ቀበርናቸው” ኡኡታውን አቀለጠው።” በማለት የተሰማውን ሃዘን አጋርቷናል። በመንግስት ግዴለሽነት ምክንያት ብቻ በደረሰው አደጋ ፣የተለያዩ ሰዎች የተለያየ አሰተያየት እየሰጡ ይገኛል

ህይወታቸውን ላጡ ፈጣሪ ነፍሳቸውን ይማር ፤ ለቤተሰቡና ለወዳጅ ዘመድ መጸናናት ፈጣሪ ይስጥልን ፤አሜን!!!

በአምቦ የጥይት ማምረቻ ፋብሪካ ውስጥ የሚፈፀም በደል ተጋለጠ source zhabesha ከሙሉነህ ዮሐንስ


ከሙሉነህ ዮሐንስ
በእውነት ምስክርነት የተዘበ ነውና በጥሞና አንብባችሁ እራሳችንን ለትግል አናዘጋጅ። ቢያንስ እንኳ እግዚአብሔር ይህን ድብቅ ያጋልጥ ብላቹህ ፀልዩ።
በጥይት ማምረቻው ውስጥ እውነት እላቹሃለሁ አንድ አንኳ የትግራይ ሰው በዕለት የማምረት ተግባሩ ውስጥ የሉበትም፡፡ ነገር ግን በሰው ኃይል ምደባ ተቆጣጣሪነት ..ወዘተ ድርሻ እነሱ እና እነሱ ብቻ ናቸው፡፡ ለምን ጥይት በማምረቱ ስራ ትግሬዎቹ የሉም? ለምትሉ መልሱ እና እውነታው ይኸውላችሁ፡-
፨፨፨ ጥይትን ለማምረት የሚጠቅመው የፖታስየም ናይትሬት ኮምፓውንድ(KNO3) /ውህድ እጅግ በጣም ለካንሰር የሚያጋልጥ በርካቶችንም ከዚህ በፊት ለሞት እና ለመካንነት የዳረገ ነው፡፡ በምሬት አንድ ወታደር ያለችኝም ይህ የማምረቱን ስራ የምንሰራው ሁላችንም ሴቶች ነን በቀን እስከ 15 ካርቶን እያንዳንዳችን እናመርታለን፡፡
አንድም የትግራይ ሴቶች የሉም። በአብዛኛው የአማራ ሴቶች ሲሆኑ ቀጥሎ የኦሮሚያና የደቡብ ናቸው፡፡ እጅግ በጣም የሚያሳዝነው ግን እያለቀሰች የነገረችኝ፦
እኔ ባጋጣሚ የትግል አጋሬን አግብቸ አንድ ሴት ልጅ ወደ ዚህ ከመግባቴ በፊት ወልጃለሁ ከቤተሰቦቸ ጋርም ትኖራለች፡፡ ሌሎች ግን የወሊድ ምርመራ ያውም በግል ሲመረመሩ ከ11 ጓደኞቸ 9ኙ በጥይት ማምረቻው የተለያዩ ኬሚካሎች ምክንያት መክነዋል። ጡቶቻቸው አካባቢ ሙሉ በሙሉ ጥላሸት/ማድያት የሚመስል መልክ አንደወጣባቸው በለቅሶ ያስረዳሉ፡፡ ምክንያቱም የሚሰሩት ያለ ሴፈቲ/የአዳጋ መከላከያ አልባሳትና ትጥቅ ስለሆነ፡፡ የሚሰጥ ወተት አንኳ ካቆመ ቆየ በማለት የአረመኔ ተግባራቸውን ሀገር ይስማው ብለው አስረድተዋል ፡፡
ለደህንነታቸው ሲባልም ነው ስማቸውንና ጠቋሚ መረጃ ያልጠቀስኩት፡፡ ታድያ ትግራዮች እውን ኢትዮጲያዊ ስሜት አላቸው፡፡ የውጭ ሀገር ዜጎች እንኳ በዚህ መልኩ የረቀቀ ዘር የማጥፋት ዘመቻ አልሰሩብንም፡፡ ወገን ስለዚህ አባባሉ የሚለው ማወቅ ስለሰዎች መኖር ነው ይላል፡፡ ስለዚህ ካወቅን የአቅማችንን ሁላችንም ወደ ትግል መግፋት አለብን፡፡ ቢያንስ እነሱን በድርጊታቸው እንኳ ልንጥላቸው ይገባል።
ቋሚ አምደኛችንን ከልብ እናመሰግናለን።