Thursday, March 16, 2017

የአርበኞች ግንቦት 7 ታጣቂዎች በሰሜን ጎንደር ዞን የተለያዩ ስፍራዎች ማክሰኞ ምሽት ጥቃት ፈጸምሁ አለ

ከአይን ምስክሮችና ከንቅናቄው ምንጮች ለመረዳት እንደተቻለው በጭልጋ፣ ደንቢያና በጎንደር ዙሪያ ወረዳዎች በተመሳሳይ ቀንና በተቀራራቢ ሰዓት በመንግስት ሃይሎችና ተቋማት ላይ ጥቃት ተፈጽሟል።

በትግል ላይ እያሉ መስዋዕትነት በከፈሉት ሻለቃ መሳፍን ጥጋቡ ወይንም ገብርዬ እንዲሁም በታጋይ ጎቤ መልኬ እና በአበራ ጎባው ስም የተሰየሙት ወታደራዊ ዘመቻዎች፣ ማክሰኞ መጋቢት 5 ፥ 2009 የመከላከያ ሰራዊት አባላትን መግደልና መቁሰል ጭምር ማስከተላቸውንም ለመረዳት ተችሏል።
ዘመቻ “ዋዋ” የሚል ስያሜ በተሰጠው በዚሁ ጥቃት ከጎንደር 80 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው በመከላከያ ሰራዊት ካምፕ ላይ ጥቃት ተሰንዝሯል። በጭልጋ ወረዳ ነጋዴ ባህር ከተማ በሰፈረው የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ በተሰነዘረ ድንገተኛ ጥቃት 3 ወታደሮች ሲገደሉ፣ 15 መቁሰላቸው ተመልክቷል። በአምስቱ ላይ የደርሰው ጉዳት ከፍተኛ በመሆኑ ጎንደር ሬፈራል ሆስፒታል ሲወስዱ፣ ቀላል ጉዳት የደርሰባቸው 7 ወታደሮች በመተማ ገንዳ ውሃ ሆስፒታል በህክምና ላይ መሆናቸውን የተገኘው ዜና ያስረዳል።
በቅርቡ በትግል ሜዳ ላይ እያሉ የተሰውትን ጎቤ መልኬን ለማስታወስም በስማቸው መጠሪያ “ዋዋ” የተሰየመው ዘመቻ ተሳታፊ የሆኑት የአርበኞች ግንቦት 7 ተዋጊዎች ጥቃቱን ፈጽመው ወደ ነበሩበት መመለሳቸው የተገለጸ ሲሆን፣ በመከላከያ ሰራዊት በኩል በቡድን መሳሪያ የተደገፈ የአጻፋ ምላሽ መሰጠቱም ተመልክቷል። በመትረየና ላውንቸር የተደገፈውን የአጸፋ ምላሽ ተከትሎ በአካባቢው ውጥረት መንገሱንና የትራንስፖርት አገልግሎት መቋረጡም ተመልክቷል።
በዚሁ በጎንደር ዞን ደንቢያ ወረዳ በተመሳሳይ ቀን ዘመቻ ገብርዬ በሚል በተሰየመው ወታደራዊ ዘመቻ በቆላ ድባ ከተማ በሚገኝ የከተማው አስተዳደር ጽ/ቤት ላይ በተከፈተ ዘመቻ የአስተዳደር ጽ/ቤቱ በከፊል ሲወድም፣ የአስተዳዳሪው መኪና መቃጠሉንም የመጣው ዜና ያስረዳል። በተመሳሳይ ጯሂት ከተማ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በካምፕነት በሚጠቀሙበት ቁጥር 2 በተባለው ጽ/ቤት ላይ በተሰነዘረ ጥቃት በወታደሮቹ ላይ የቃጠሎ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
በአብራጅራ ከተማ አብራጅ ጽ/ቤት በሰፈሩ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ እንዲሁም በቸንከር ቀበሌ የከተማዋ ኮማንድ ፖስት ማዘዣ ላይ ጥቃት ተፈጽሟል። በጥቃቱ የቸንከር ቀበሌ ኮማንድ ፖስት ማዘዣ ጣቢያ ሲወድም፣ አንድ የኮማንድ ፖስቱ አባል መጎዳቱንና አንድ መጋዘን መቃጠሉን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።
በሰሜን ጎንደር አካባቢዎች መሳሪያ አንስተው በትግል ላይ ከነበሩት አንዱ በነበረውና መስዋዕትነት በከፈለው በአበራ ጎባው ስም በተመሳሳይ ቀን በጎንደር ዙሪያ የአርበኞች ግንቦት 7 ሃይሎች ጥቃት መፈጸማቸውም ተመልክቷል።
የአርበኞች ግንቦት 7 ተዋጊዎች ማክሰኞ መጋቢት 5 ፥ 2009 እኩለ ሌሊት አካባቢ በጎንደር ዙሪያ ወረዳ በደጋማ ከተማ በወህኒ ቤት እንዲሁም ኮማንድ ፖስቱ በሚጠቀምባቸው ቢሮዎች ላይ ጥቃት መፈጸሙ ታውቋል። እንዲሁም የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል በሆኑት በአቶ ደሴ ዘገየ መኖሪያ ቤት ላይም ተመሳሳይ ጥቃት መከተሉንም የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።

Wednesday, March 15, 2017

ለሥልጠና ወደ አድዋ የተወሰዱ የወልቃይት ዐማሮች በድብደባ ጉዳት ደረሰባቸው ከሙሉቀን ተስፋው source zhabesha


ከሙሉቀን ተስፋው
የ10ኛ ክፍል ትምህርታቸውን የጨረሱ የወልቃይት ወጣቶችን አሰልጥኜ ሥራ አስይዛችኋለሁ በማለት ነበር ሕወሓት ወደ አድዋ የወሰዳቸው፡፡ ከወልቃይትና ጠገዴ አካባቢዎች ተመልምለው የተወሰዱ ወጣቶች አድዋ ሲደርሱ ግን የጠበቁትን ሥልጠና አላገኙም፡፡
አብረዋቸው በሚማሩ የትግራይ ተማሪዎችና አስተማሪዎች ‹‹ስለምን ዐማራ ነን አላችሁ፤ ትግሬ የተጠላው በእናንተ ምክንያት ነው!›› የሚል ወከባና ጥያቄ ይደርስባቸዋል፡፡ ከዚያ ወጣቶቹ ‹‹ታዲያ ምን ልንል ነው፤ እኛ እኮ ዐማራ ነን›› የሚል የማያወላዳ ምላሽ ይሰጣሉ፡፡
ትናንት መጋቢት 5 ቀን 2009 ዓ.ም ለሥልጠና የሔዱት ሁሉም ወጣቶች ያለምንም ረዳት በሰው አገር የተደበደቡ ሲሆን ሐጂ የተባለ ወጣት ከፍተኛ የአከርካሪ ጉዳት ደርሶበታል ተብሏል፡፡ በድብደባው ጉዳት የደረሰባቸው ዐማሮች እስካሁን ምንም ዓይነት ሕክምና ካለማግኘታቸውም በተጨማሪ ወደ ወልቃይት እንዳይመለሱ ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገባቸው ነው ተብሏል፡፡ ወደ ወልቃይት ከተመለሱ ለበለጠ አደጋ እንደሚጋለጡና እንደሚታሰሩም ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡

ኖርን እና ሞትን! Posted by: Zehabesh 

ኖርን እና ሞትን!










Tuesday, March 14, 2017

መንግስታዊ ቸልተኝነት እና ብሔራዊ የሐዘን ቀን! – (ይድነቃቸው ከበደ) source zhabesha


መንግስት በደረሰበት ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዲሁም ፣ በማህበራዊ ድረ ገጾች በተለያየ መንገድ ይደረግ የነበረው ቅስቀሳ ባሳደረው ግፊት፣ ብሔራዊ የሐዘን ቀን በኢትዮጵያ ሊታወጅ ችሏል።በዚህም መሰረት ፣ ከመጋቢት 3 እስከ መጋቢት 5 ቀን 2009 ዓ.ም ለሦስት ቀን ብሔራዊ የሃዘን ቀን እንዲሆን ተወስኖል።

በመንግስት ግዴለሽነት ምክንያት ብቻ ! በደረሰው የቆሻሻ ክምር መናድ ፣ከ75 ሰው የማያንስ ለሞት የተዳረገ ሲሆን በመቶ የሚቆጠሩ ለከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት ተዳርገዋል ። እንዲሁም ከ250 የማያንሱ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ሲሆን በጊዚያዊ መጠለያ እንዲቆዩ ተደርጓል ። በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የደረሰው አደጋ፣ የዓለማችን ታላላቅ የመገናኛ ብዙሃን በፊት ገጻቸው ሰፊ የዜና ሽፍና ሰጥተውታል ።

መንግስት አደጋው ከደረሰ ከሦስት ቀን በኋላ ፣ በደረሰበት ከፍተኛ ግፊትና ተጽዕኖ ብሔራዊ የሐዘን ቀን ከማወጁ በፊት ፣ በአዲስ አበባ የጀርምን ኢምባሲ በደረሰው አደጋ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን በመግለጽ ፣ በኢምባሲው የጀርመን እና የአውሮፓ ህብረት ባንዲራ ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ በማድረግ ለኢትዮጵያውያን የጀርመን መንግስት አጋርነቱን አሳይቷል ። ዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ተቋማት ፣በደረሰው አደጋ ማዘናቸውን በመግለጽ ፣ ለአደጋው መንስኤ መንግስትን ተጠያቂ አድርጓል ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ፣የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ፣ አደጋው በደረሰበት አካባቢ በመሄድ ፣ የሟች ቤተሰቦችን እያጽናኑ የሚገኝ ሲሆን፣ ከነፍስ አድን ሰራተኞች ጋር በመተባበር ፣ በቆሻሻ ክምር ውስጥ በህይወት የተረፈ እና ጉዳት የደረሰባቸውን በማፈላለግ ላይ ይገኛሉ። አደጋው በተከሰተበት ቦታ የተገኘው የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ወንድም ፣ አቶ ታሪኩ ደሳለኝ (ሚኪ) በቦታው ተገኝቶ በማህበራዊ ድረ ገጹ እንደገለጸው ከሆነ ፣ “ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የሞቱት ነብስ ይማራ ለማለት ቤተሰቦቻቸውን ለማፅናናት ተገኝቻለሁ። በየአምስት ሜትሩ ድንኳን ተተክሎ ማየት ያሰደነግጣል። አንዳንዱ ጋር ለሦስት ለአራተ ሰው በአንድ ድንኳን ሀዘን ተቀምጠዋል። አሁንም ከቆሻሻው ክምር አስክሬን እየወጣ ነው። እኔ ከደረስኩበት ከ12 እስከ 3 ሰዓት ብቻ 12 አስክሬኖች ወጥተዋል። ነዋሪዎቹ እንደሚናገሩት ይሄ ከላይ ያለው ናዳ ቆሻሻ ውስጥ የተገኙ ናቸው ገና የታቸኛወ ውስጥ ይቀራል ብለዋል። አሁንም ውሃ መብራት የለም።አሁንም በዙ ሰው አልወጣም ብዙዎች ያለመጠለያ ቀርተዋል።የተቻላችሁን የሀል ድግፍ እንድታደርግ “በማለት የተሰማውን ገልጸዋል ።

ሌላው የዓይን እማኝ የሆነው ጋዜጠኛ ጌጡ ተመስገን ፣ በትላንትናው ዕለት በተካሄደው የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተገኝቶ ሃሳብን እንደሚከተለው ገልጸዋል ።”50ዎቹ በደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል ። የሟቾቹ ቁጥር 65
ደርሷል። ፍለጋው እንደቀጠለ ነው። ከሟቾቹ ውስጥ የአንድ ቤት አምስት የቤተሰብ አባላት ይገኙበታል ። ኮልፌ እስላም መቃብር ሀዘንተኛው ነስሩ ሁሴን ተጠጋሁት፣ “እህቴን፣ የእህቴ ሁለት ልጆች፣ የወንድሜ ሚስት ከነልጇ ይሄው ቀበርናቸው” ኡኡታውን አቀለጠው።” በማለት የተሰማውን ሃዘን አጋርቷናል። በመንግስት ግዴለሽነት ምክንያት ብቻ በደረሰው አደጋ ፣የተለያዩ ሰዎች የተለያየ አሰተያየት እየሰጡ ይገኛል

ህይወታቸውን ላጡ ፈጣሪ ነፍሳቸውን ይማር ፤ ለቤተሰቡና ለወዳጅ ዘመድ መጸናናት ፈጣሪ ይስጥልን ፤አሜን!!!

በአምቦ የጥይት ማምረቻ ፋብሪካ ውስጥ የሚፈፀም በደል ተጋለጠ source zhabesha ከሙሉነህ ዮሐንስ


ከሙሉነህ ዮሐንስ
በእውነት ምስክርነት የተዘበ ነውና በጥሞና አንብባችሁ እራሳችንን ለትግል አናዘጋጅ። ቢያንስ እንኳ እግዚአብሔር ይህን ድብቅ ያጋልጥ ብላቹህ ፀልዩ።
በጥይት ማምረቻው ውስጥ እውነት እላቹሃለሁ አንድ አንኳ የትግራይ ሰው በዕለት የማምረት ተግባሩ ውስጥ የሉበትም፡፡ ነገር ግን በሰው ኃይል ምደባ ተቆጣጣሪነት ..ወዘተ ድርሻ እነሱ እና እነሱ ብቻ ናቸው፡፡ ለምን ጥይት በማምረቱ ስራ ትግሬዎቹ የሉም? ለምትሉ መልሱ እና እውነታው ይኸውላችሁ፡-
፨፨፨ ጥይትን ለማምረት የሚጠቅመው የፖታስየም ናይትሬት ኮምፓውንድ(KNO3) /ውህድ እጅግ በጣም ለካንሰር የሚያጋልጥ በርካቶችንም ከዚህ በፊት ለሞት እና ለመካንነት የዳረገ ነው፡፡ በምሬት አንድ ወታደር ያለችኝም ይህ የማምረቱን ስራ የምንሰራው ሁላችንም ሴቶች ነን በቀን እስከ 15 ካርቶን እያንዳንዳችን እናመርታለን፡፡
አንድም የትግራይ ሴቶች የሉም። በአብዛኛው የአማራ ሴቶች ሲሆኑ ቀጥሎ የኦሮሚያና የደቡብ ናቸው፡፡ እጅግ በጣም የሚያሳዝነው ግን እያለቀሰች የነገረችኝ፦
እኔ ባጋጣሚ የትግል አጋሬን አግብቸ አንድ ሴት ልጅ ወደ ዚህ ከመግባቴ በፊት ወልጃለሁ ከቤተሰቦቸ ጋርም ትኖራለች፡፡ ሌሎች ግን የወሊድ ምርመራ ያውም በግል ሲመረመሩ ከ11 ጓደኞቸ 9ኙ በጥይት ማምረቻው የተለያዩ ኬሚካሎች ምክንያት መክነዋል። ጡቶቻቸው አካባቢ ሙሉ በሙሉ ጥላሸት/ማድያት የሚመስል መልክ አንደወጣባቸው በለቅሶ ያስረዳሉ፡፡ ምክንያቱም የሚሰሩት ያለ ሴፈቲ/የአዳጋ መከላከያ አልባሳትና ትጥቅ ስለሆነ፡፡ የሚሰጥ ወተት አንኳ ካቆመ ቆየ በማለት የአረመኔ ተግባራቸውን ሀገር ይስማው ብለው አስረድተዋል ፡፡
ለደህንነታቸው ሲባልም ነው ስማቸውንና ጠቋሚ መረጃ ያልጠቀስኩት፡፡ ታድያ ትግራዮች እውን ኢትዮጲያዊ ስሜት አላቸው፡፡ የውጭ ሀገር ዜጎች እንኳ በዚህ መልኩ የረቀቀ ዘር የማጥፋት ዘመቻ አልሰሩብንም፡፡ ወገን ስለዚህ አባባሉ የሚለው ማወቅ ስለሰዎች መኖር ነው ይላል፡፡ ስለዚህ ካወቅን የአቅማችንን ሁላችንም ወደ ትግል መግፋት አለብን፡፡ ቢያንስ እነሱን በድርጊታቸው እንኳ ልንጥላቸው ይገባል።
ቋሚ አምደኛችንን ከልብ እናመሰግናለን።

Saturday, March 11, 2017

ድርቁ መቶ ሺዎችን አፈናቅሏል፤ ከ250 ሺ በላይ ህፃናት ትምህርት አቋርጠዋል


Image result for ethiopian drought 2017


ድርቁን ተከትሎ አስከፊ ረሀብ ሊከሰት እንደሚችል ተመድ አስጠንቅቋል
መንግሥት የእርዳታ ጥሪ ቢያቀርብም እስካሁን ምላሽ አላገኘም
እስከ 15 ሺህ ብር ይሸጡ የነበሩ ከብቶች፣ 500 ብር ድረስ እየተሸጡ ነው
Addis Admass
በኦሮሚያና በሶማሌ ክልል የድርቅ አደጋ በመቶ ሺዎች የሚገመቱ ሰዎችን ያፈናቀለ ሲሆን ከሩብ ሚሊዮን በላይ ህፃናት ትምህርታቸውን እንዲያቋርጡ ውጪ ማድረጉንም የተባበሩት መንግስታት የእርዳታና የሰብአዊ ድጋፍ ድርጅት (UNOCHA) ሰሞኑን ባወጣው ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡
በሌላ በኩል በድርቅ ከተጎዱ አካባቢዎች አንዱ በሆነው የኦሮሚያ ክልል፣ ቦረና ዞን ያሉ አርሶ አደሮች በህይወት የተረፉ ከብቶቻቸውን በርካሽ ዋጋ እየሸጡ መሆኑን ምንጮች ለአዲስ አድማስ ጠቁመዋል፡፡
ድርቅ ባጠቃቸው የቦረና አካባቢዎች በጉዳዩ ላይ ጥናት በማድረግ ላይ የሚገኙ ባለሙያዎች እንደሚሉት፤ በደህናው ጊዜ እስከ 15 ሺህ ብር ይሸጡ የነበሩ በሬዎች፤ በአሁን ወቅት ከ500 እስከ 1 ሺህ ብር ድረስ እየተሸጡ ሲሆን ከ500 እስከ 1 ሺህ 500 ብር ይሸጡ የነበሩ በጎችና ፍየሎች ደግሞ በ80 እና በ90 ብር እየተሸጡ ነው ተብሏል፡፡
ከብቶቹ በአብዛኛው በአካላዊ ቁመናቸው የተጎዱ በመሆኑ፣ ፈላጊ ስለሌላቸው አርብቶ አደሮቹ በርካሽ ዋጋ ለመሸጥ መገደዳቸውን ባለሙያዎቹ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡፡፡
የከብቶች ሞትም እንደቀጠለ መሆኑን የጠቆሙት አጥኚዎች በተለይ የመጠጥ ውሃ ችግሩ ተባብሶ መቀጠሉን ገልፀው፤ መንግስት በቦቴ ውሃ እያቀረበ ቢሆንም በበቂ መጠን አለመሆኑን አመልክተዋል፡፡
ወቅታዊ ሪፖርቱን ሰሞኑን ይፋ ያደረገው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በበኩሉ፤ በተለይ በኦሮሚያና በሶማሌ ክልል የሚሊዮኖችን ህይወት አደጋ ላይ ለጣለው ድርቅ መንግስትና የእርዳታ ለጋሽ ተቋማት ውሃና ምግብ በማቅረብ እየተረባረቡ ቢሆንም ከአደጋው አስከፊነት አንፃር በቂ አይደለም ብሏል፡፡
በድርቁ ምክንያት 228 ሺህ ህፃናት ትምህርት ማቋረጣቸውን ይፋ ያደረገው ሪፖርቱ፤ ከእነዚህ ውስጥ 183 ሺህ 090 የሶማሌ ክልል ህፃናት ሲሆኑ 44 ሺህ 571 የሚሆኑት ደግሞ የኦሮሚያ ክልል መሆናቸውን ጠቁሟል፡፡ በሁለቱ ክልሎች ማለትም በኦሮሚያ በድርቁ ምክንያት 141 ት/ቤቶች፣ በሶማሌ ክልል 437 ት/ቤቶች በድምሩ 578 ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውን ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡
ምግብና ውሃ ፍለጋ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አባወራዎች ከቀዬአቸው መፈናቀላቸውን የጠቆመው የተመድ የእርዳታና ሰብአዊ ድጋፍ ድርጅት ሪፖርቱ፤ ከተፈናቀሉት ውስጥ 163 ሺህ ያህሉ ለትምህርት የደረሱ ህፃናት መሆናቸውን አመልክቷል፡፡ እነዚህን ተፈናቃይ ህፃናት ለ75 ቀናት ሊመመገብ 5.9 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግም ተገልጿል፡፡
በእርዳታ አሰጣት ደንብ ለአንድ ሰው በቀን ውስጥ 5 ሊትር ውሃ መቅረብ ያለበት ቢሆንም በአሁን ወቅት ለአንድ ሰው በቀን እየቀረበ ያለው በአማካይ 2.1 ሊትር ውሃ መሆኑን የተመድ ሪፖርት ጠቁሞ፤ የውሃ ክፍፍሉም ፍትሃዊ አለመሆኑንና ከወረዳ ወረዳ እንደሚለያይ አስታውቋል፡፡
በአጠቃላይ ለ5.6 ሚሊዮን የተረጂዎች 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ እርዳታ እንደሚያስፈልግና ይህ እርዳታ በአፋጣኝ ካልተገኘ ሁኔታው ወደ አስከፊ ረሃብ ሊቀየር እንደሚችል አሳስቧል፡፡
ተመድ መንግስት ከለጋሽ ድርጅቶች ጋር በመሆን የእርዳታ ርብርብ እያደረጉ ነው ቢልም መንግስት በበኩሉ፤ ለድርቁ አደጋ የእርዳታ ጥሪ ቢያቀርብም እስካሁን ምላሽ አለማግኘቱን አስታውቋል፡፡
በሌላ በኩል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አፍሪካን በተመለከተ ባወጣው ሪፖርቱ፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ በድርቅ በተጎዱ፣ ከሠሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሃገራት፣ በአሁኑ ወቅት ከ20 ሚሊዮን በላይ ሰዎች አስቸኳይ የእርዳታ ርብርብ እንደሚፈልጉ አስታውቆ፤ አለማቀፉ ማህበረሠብ እጁን እንዲዘረጋ ጥሪውን አስተላልፏል

ብአዴን የህውሃት የትሮይ ፈረስ – (በቬሮኒካ መላኩ )

በቬሮኒካ መላኩ
……………………
ሰሞኑን የትግሬ ብሄርተኞች ” ብአዴን እንደዚህ አለ እንደዚያ አለ ” እየተባለ ሴቱ በየወፍጮ ቤቱ ወንዱም በየቀንዶ ቤቱ እያወራ እየፈነጠዘ ነው ።
ለአማራ ህዝብ ብአዴን የሚባል ድርጅት ባእዱ ነዉ ። የአማራ ህዝብ ብአዴን አማረኛ ተናጋሪ ህወሀት ናቸሁ ተላላኪ ናቸሁ ብሎ ፊቱን ካዞረባቸው ብዙ አመታት ተቆጠረ ።
ብአዴን ሲጠሩት አቤት ሲልኩት ወዴት የሚል የሆዳሞች ስብስብ የህዋት ተላላኪ ድርጅት ነው ተብሎ አቋም የተያዘበት ድርጅት እንደሆነ የአደባባይ ሚስጥር ነው ። መቸም ትግሬዎች በራሳችሁ አምሳል ጠፍጥፋችሁ የሰራችኋቸውነን ተላላኪዎቻችሁን እያወቃችሁ ብአዴን እንዲህ አለ እያላችሁ ጮቤ ምትረግጡት እና ህዝቡን ለመሸወድ የምትሞክሩት ነገር አስገራሚም አስቂኝም ነው።
እንደት ትግሬ የራሱን ድምፅ እንደገደል ማሚቶ ኤኮ እያደረገ መልሶ በሚዲያው መስማቱ እንደት ሊያስፈነጥዘው ቻለ? ይሄ የሰዎቹን ንቃተ ህሊና የት ደረጃ እንደደረሰ አመላካች ስለሆነ አይገርምም ።

“ብአዴን ማነው ? ” የሚል ጥያቄ በማንሳት አንባቢን ማዛግ የሚያስፈልግ አይመስለኝም ። ነገር ግን አንዳንድ ጥያቄዎችን ማንሳት ጥሩ ይመስለኛል ።
ለመሆኑ ግማሽ ትግሬው እና የአማራን ህዝብ በፀያፍ ስድቡ የዘለፈው አለምነው መኮንን እንዴት ለአማራ ሊያስብ ይችላል?
የትግሬ ተወላጁ ካሳ ተ/ብርሀን እንዴት ለአማራ መሬት ሊጨነቅ ይችላል? ኤርትራዊው በረከት ስሞን እንዴት የሚጠላውን አማራ ሊያስብለት ይችላል?
የእድሜውን ከግማሽ በላይ ሀረር እና ትግራይ ውስጥ ሲርመጠመጥ ያሳለፈው እና ትግሪኛ ተናጋሪው አዲሱ ለገሰ በምንም ተአምር ለአማራ ሊቆረቆር ይችላል?
ትግሬው ህላዊ ዮሴፍ እንደት ለአማራ ሊጨነቅ ይችላል?
የትግሬን የአምባሻ ዱቄት ተሸከም ቢሉት የማያቅማማው ሎሌ ደመቀ መኮንን እንደት አማራን ሊወክል ይችላል?

የአማራ ህዝብ ብአዴን ወልቃይት እና ሌሎች በማን አለብኝነት የተወሰዱ የአማራ መሬቶች ማስመለስ እንደማይችል አሳምሮ ያውቀዋል። ማስመለስ ቢችልማ መጀመሪያውን እንዴት አሳልፎ ይሰጥ ነበር?

አዲሱ ለገሰ የተባለው የህውሃት ሎሌ በወልቃይት ጉዳይ ላይ ባደረገው ኢንተርቪው ሳያስበው አንድ እውነት አምልጦታል ። Smart ብትሆኑ ኖሮ የሰውየው ንግግር ሊያሳዝናችሁ እንጅ ሊያስፈነጥዛችሁ ባልተገባ ነበር ። ሎሌ አዲሱ ለገሰ ምን አለ ? ” የወልቃይት ጉዳይን የብአዴን ጥያቄ አይደለም አለ ።” እውነቱን ነው ። ከመነሻውም የወልቃይት ጥያቄ የ 40 ሚሊዮን የአማራ ወልቃይት ህዝብ ጥያቄ እንጂ ብአዴን የተባለው ድርጅት ጥያቄ አልነበረም ። የአማራ ህዝብ እኮ እየታጋለ ያለው ህውሃትን ብቻ ሳይሆን አማርኛ ተናጋሪ የህውሃት ክንፍ የሆነውን ብአዴንንም ጭምር ነው ።

ባለፉት 25 አመታት የወልቃይት ህዝብ እያለ ያለው ጨዋታው በየብሄርህ ከሆነ እኛን ለምን ከብሄራችን ትነጥሉናላችሁ ነው። ይሄ ደግሞ መብታቸው ነው። ቋንቋቸውን ባህላቸውን ለመጠበቅ ወደ ክልላቸው መመለስ አለባቸው።
የወያኔ አስተዳደር ስምምነት ይሄው ስለሆነ የወልቃይት ህዝብ ማንነቱን ከመሬቱ ጋር ኣያይዞ እየጠየቀ ስለሆነ መመለስ አለበት።
ዘረኛው ወያኔ አልተረዳውም እንጂ የትግራይ ህዝብ ድንበሩ ተከዜም ወልቃይትም አልነበረመም። ድንበሩ ከኢሉባቦር እስከ ኦጋዴን እስከ ሞያሌ እስከ ባድመ ነው። ነገር ግን ወያኔ የዘር ጨዋታውን ፊሽካ በማስነፋት ስለጀመረው በስግብግብነት እንደ አሳማ ከጎንደር እና ከወሎ የዋጠውን መሬት ማንቁርቱን ተይዞ መትፋቱ አይቀርም ። በመጀመሪያ በዚህ ጉዳይ ላይ ወደ ስምምነት መምጣት አለባት። ሁላችን ወሰናችን ይሄ መሆኑን መስማማት አለብን። አለበለዚያ ወያኔ በአንድ በኩል የቋንቋ መንግስት አምሮት በሌላ በኩል ደግሞ ትንሽ ለም መሬት ሲያይ ከቤንሻንጉልም ከአማራም ቦጨቅ ማድረግ እያማረው ኣይሆንም። ትክክልም አይደለም።

በብዙ መልኩ ስንገመግመው የትግሬ ወያኔ ባህሪ የክረምት ጅብ አይነት ነው ።
በአንድ በኩል በትግሬ ውስጥ ያሉ ሃብቶችን የኢፈርትንም ጭምር ፣ተፈጥሮ ሃብቱንም የኛ የትግራይ ህዝብ ብቻ ነው ይልና በአንድ እጁ ይዞ ይታያል። ንብረትነቱ የኛ ብቻ ነው ይላል። በሌላ በኩል ደግሞ የአባይን ወንዝ ፣ የጣናን ተፋሰስ እና ለም መሬት ፣ የጉጂዎችን ወርቅ ፣የጅማውን ቡና የሁላችን በማለት አብሮ ይበላል። የሌላውን በአንድ ገበታ አርገን እንብላ ይልህና የራሱን ብቻውን ይውጣል ። የራሱን በጁ ይዞ እያደለበ የሌላውን ያጫርሳል። ይሄ ጥሩ አይደለም። ለሃቹ ለሃገራችን ኣይበጅም። ብንገነጠልም እንኳን ለጉርብትና አይሆነንም። ታሪካዊ እሴቱም ጥሩ ኣይደለም።

የአማራ ህዝብም ሆነ የሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ባለፉት ወራቶች ጥያቄውን በግልፅ አስቀምጧል፡፡ ይህም ከተከዜ ማዶ ያለን ቦታ ለጎንደር መመለስን ጨምሮ የህወሃትን የበላይነት፣ ጣልቃ ገብነትና ዝርፊያ ጨርሶ መቆምንም ይጨምራል፡፡ ይህን በመናቅ ግን ጥያቄውን ሳይመልሱ መቅረት በጉልበት መሞከር ሁኔታውን የሚያብስ ሲሆን በሚሊዮን የሚቆጠር ሀይል እንኳ ቢኖራቸሁ ህዝብን ማሸነፍ እንኳን በእውን በህልማችሁ እንኳን ሊሳካላቸውሁ የማይችል ጉዳይ ነው፡፡ ይህ ዘመን እንዳለፉት 25 አመታት አይደለም። አማራ አሁን ከልሂቅ እስከ ደቂቅ ሁሉንም ያውቃል ። ወቅቱ እጅግ የተለየና ለህዝብ ምቹ የሆነ ሲሆን የፈለገውን ያህል አጋዚ ያሰማራ በመጨረሻ ላይ ግን ዘመኑ የወያኔን ፍፃሜ ማብሰሪያ ዘመን የሚሆን ነው፡፡

ወያኔ እና መሰሎቹ አንድ መገንዘብ ያለባቸው ነገር አለ ። ጥያቄዎች በሰላም መንገድ ካልተፈቱ ስንፋጅና ስንጎዳዳ ኖረን ወያኔ በጉልበት እንደወሰደው ሁሉ ከነወለዱ በጉልበት ይመለሳል ።

ማጠቃለያ
የአማራ ህዝብ ምን ማድረግ አለበት?

1~ የአማራ ህዝብ በታሪክ ታይቶ በማያውቅ ሁኔታ የተጋረጠበትን ችግር ለመፍታት እርስ በእርስ መረጃ እየተለዋወጡ በወንድማማችነት መንፈስ መደራጀት ያስፈልጋል ።አማራ በማንም እንዳይጠቃ እርስ በርስ እየተጠባበቁና እየተከላከሉ ወንድማማችነትን ማዳበር ።

2~ የገበሬውን ነገር አደራ፡፡ ከማንኛውም ጊዜ በበለጠ ሁኔታ በመረጃ እያጠነከሩ በስራው መበርታት ይኖርብታል፡፡
ዛሬ ካልተሰራና ነገ ካልተመረተ ከነገ ወዲያ ችግር ሲፈጠር ህወሃት በእርዳታ መልክ የፖለቲካም ሆነ የኢኮኖሚ ጥገኛ ለማድረግ እንዳትችል ዛሬውኑ ሁሉም በእጃችን ያለና የሚቻል ስለሆነ ሁሉም በያለበት በስራ መበርታት አለበት፡፡ በስራ የሚበረታና ራሱን የሚችል ህዝብ ምን ጊዜም አሸናፊ መሆኑ ታወቆ አርሶ አደሩ በስራው እንድበረታ መርዳት ።

3 ~ሌላው ቁልፍ ነጥብ የአማራ ቲቪ እንደ OMN መቁዋቋም አለበት።
አባቶቻችን ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው ያሉት ትልቅ ስትራቴጂ ነው ።”ህዝቤ እውቀት በማጣት ጠፋ” ይላል ነብዩ ሆሴ።ያማራ ህዝብ የጠፋው እውቀት፣መረጃ፣ በማጣቱ ነው።መረጃ የደምስር ነው።መረጃ የሌለው ማህበረሰብና ከባህር እንደ ወጣ አሳ መጨረሻቸው “ሞት” ነው ። አማራ ለህዝቡ መረጃ የሚሰጠው የራሱ የሆነ ሚዲያ እንደሚያስፈልግ ታውቆ ለተግባራዊነቱ ጥረት ማድረግ ።
ልብ ያለው ልብ ይበል!