Saturday, March 11, 2017

ድርቁ መቶ ሺዎችን አፈናቅሏል፤ ከ250 ሺ በላይ ህፃናት ትምህርት አቋርጠዋል


Image result for ethiopian drought 2017


ድርቁን ተከትሎ አስከፊ ረሀብ ሊከሰት እንደሚችል ተመድ አስጠንቅቋል
መንግሥት የእርዳታ ጥሪ ቢያቀርብም እስካሁን ምላሽ አላገኘም
እስከ 15 ሺህ ብር ይሸጡ የነበሩ ከብቶች፣ 500 ብር ድረስ እየተሸጡ ነው
Addis Admass
በኦሮሚያና በሶማሌ ክልል የድርቅ አደጋ በመቶ ሺዎች የሚገመቱ ሰዎችን ያፈናቀለ ሲሆን ከሩብ ሚሊዮን በላይ ህፃናት ትምህርታቸውን እንዲያቋርጡ ውጪ ማድረጉንም የተባበሩት መንግስታት የእርዳታና የሰብአዊ ድጋፍ ድርጅት (UNOCHA) ሰሞኑን ባወጣው ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡
በሌላ በኩል በድርቅ ከተጎዱ አካባቢዎች አንዱ በሆነው የኦሮሚያ ክልል፣ ቦረና ዞን ያሉ አርሶ አደሮች በህይወት የተረፉ ከብቶቻቸውን በርካሽ ዋጋ እየሸጡ መሆኑን ምንጮች ለአዲስ አድማስ ጠቁመዋል፡፡
ድርቅ ባጠቃቸው የቦረና አካባቢዎች በጉዳዩ ላይ ጥናት በማድረግ ላይ የሚገኙ ባለሙያዎች እንደሚሉት፤ በደህናው ጊዜ እስከ 15 ሺህ ብር ይሸጡ የነበሩ በሬዎች፤ በአሁን ወቅት ከ500 እስከ 1 ሺህ ብር ድረስ እየተሸጡ ሲሆን ከ500 እስከ 1 ሺህ 500 ብር ይሸጡ የነበሩ በጎችና ፍየሎች ደግሞ በ80 እና በ90 ብር እየተሸጡ ነው ተብሏል፡፡
ከብቶቹ በአብዛኛው በአካላዊ ቁመናቸው የተጎዱ በመሆኑ፣ ፈላጊ ስለሌላቸው አርብቶ አደሮቹ በርካሽ ዋጋ ለመሸጥ መገደዳቸውን ባለሙያዎቹ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡፡፡
የከብቶች ሞትም እንደቀጠለ መሆኑን የጠቆሙት አጥኚዎች በተለይ የመጠጥ ውሃ ችግሩ ተባብሶ መቀጠሉን ገልፀው፤ መንግስት በቦቴ ውሃ እያቀረበ ቢሆንም በበቂ መጠን አለመሆኑን አመልክተዋል፡፡
ወቅታዊ ሪፖርቱን ሰሞኑን ይፋ ያደረገው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በበኩሉ፤ በተለይ በኦሮሚያና በሶማሌ ክልል የሚሊዮኖችን ህይወት አደጋ ላይ ለጣለው ድርቅ መንግስትና የእርዳታ ለጋሽ ተቋማት ውሃና ምግብ በማቅረብ እየተረባረቡ ቢሆንም ከአደጋው አስከፊነት አንፃር በቂ አይደለም ብሏል፡፡
በድርቁ ምክንያት 228 ሺህ ህፃናት ትምህርት ማቋረጣቸውን ይፋ ያደረገው ሪፖርቱ፤ ከእነዚህ ውስጥ 183 ሺህ 090 የሶማሌ ክልል ህፃናት ሲሆኑ 44 ሺህ 571 የሚሆኑት ደግሞ የኦሮሚያ ክልል መሆናቸውን ጠቁሟል፡፡ በሁለቱ ክልሎች ማለትም በኦሮሚያ በድርቁ ምክንያት 141 ት/ቤቶች፣ በሶማሌ ክልል 437 ት/ቤቶች በድምሩ 578 ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውን ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡
ምግብና ውሃ ፍለጋ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አባወራዎች ከቀዬአቸው መፈናቀላቸውን የጠቆመው የተመድ የእርዳታና ሰብአዊ ድጋፍ ድርጅት ሪፖርቱ፤ ከተፈናቀሉት ውስጥ 163 ሺህ ያህሉ ለትምህርት የደረሱ ህፃናት መሆናቸውን አመልክቷል፡፡ እነዚህን ተፈናቃይ ህፃናት ለ75 ቀናት ሊመመገብ 5.9 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግም ተገልጿል፡፡
በእርዳታ አሰጣት ደንብ ለአንድ ሰው በቀን ውስጥ 5 ሊትር ውሃ መቅረብ ያለበት ቢሆንም በአሁን ወቅት ለአንድ ሰው በቀን እየቀረበ ያለው በአማካይ 2.1 ሊትር ውሃ መሆኑን የተመድ ሪፖርት ጠቁሞ፤ የውሃ ክፍፍሉም ፍትሃዊ አለመሆኑንና ከወረዳ ወረዳ እንደሚለያይ አስታውቋል፡፡
በአጠቃላይ ለ5.6 ሚሊዮን የተረጂዎች 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ እርዳታ እንደሚያስፈልግና ይህ እርዳታ በአፋጣኝ ካልተገኘ ሁኔታው ወደ አስከፊ ረሃብ ሊቀየር እንደሚችል አሳስቧል፡፡
ተመድ መንግስት ከለጋሽ ድርጅቶች ጋር በመሆን የእርዳታ ርብርብ እያደረጉ ነው ቢልም መንግስት በበኩሉ፤ ለድርቁ አደጋ የእርዳታ ጥሪ ቢያቀርብም እስካሁን ምላሽ አለማግኘቱን አስታውቋል፡፡
በሌላ በኩል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አፍሪካን በተመለከተ ባወጣው ሪፖርቱ፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ በድርቅ በተጎዱ፣ ከሠሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሃገራት፣ በአሁኑ ወቅት ከ20 ሚሊዮን በላይ ሰዎች አስቸኳይ የእርዳታ ርብርብ እንደሚፈልጉ አስታውቆ፤ አለማቀፉ ማህበረሠብ እጁን እንዲዘረጋ ጥሪውን አስተላልፏል

ብአዴን የህውሃት የትሮይ ፈረስ – (በቬሮኒካ መላኩ )

በቬሮኒካ መላኩ
……………………
ሰሞኑን የትግሬ ብሄርተኞች ” ብአዴን እንደዚህ አለ እንደዚያ አለ ” እየተባለ ሴቱ በየወፍጮ ቤቱ ወንዱም በየቀንዶ ቤቱ እያወራ እየፈነጠዘ ነው ።
ለአማራ ህዝብ ብአዴን የሚባል ድርጅት ባእዱ ነዉ ። የአማራ ህዝብ ብአዴን አማረኛ ተናጋሪ ህወሀት ናቸሁ ተላላኪ ናቸሁ ብሎ ፊቱን ካዞረባቸው ብዙ አመታት ተቆጠረ ።
ብአዴን ሲጠሩት አቤት ሲልኩት ወዴት የሚል የሆዳሞች ስብስብ የህዋት ተላላኪ ድርጅት ነው ተብሎ አቋም የተያዘበት ድርጅት እንደሆነ የአደባባይ ሚስጥር ነው ። መቸም ትግሬዎች በራሳችሁ አምሳል ጠፍጥፋችሁ የሰራችኋቸውነን ተላላኪዎቻችሁን እያወቃችሁ ብአዴን እንዲህ አለ እያላችሁ ጮቤ ምትረግጡት እና ህዝቡን ለመሸወድ የምትሞክሩት ነገር አስገራሚም አስቂኝም ነው።
እንደት ትግሬ የራሱን ድምፅ እንደገደል ማሚቶ ኤኮ እያደረገ መልሶ በሚዲያው መስማቱ እንደት ሊያስፈነጥዘው ቻለ? ይሄ የሰዎቹን ንቃተ ህሊና የት ደረጃ እንደደረሰ አመላካች ስለሆነ አይገርምም ።

“ብአዴን ማነው ? ” የሚል ጥያቄ በማንሳት አንባቢን ማዛግ የሚያስፈልግ አይመስለኝም ። ነገር ግን አንዳንድ ጥያቄዎችን ማንሳት ጥሩ ይመስለኛል ።
ለመሆኑ ግማሽ ትግሬው እና የአማራን ህዝብ በፀያፍ ስድቡ የዘለፈው አለምነው መኮንን እንዴት ለአማራ ሊያስብ ይችላል?
የትግሬ ተወላጁ ካሳ ተ/ብርሀን እንዴት ለአማራ መሬት ሊጨነቅ ይችላል? ኤርትራዊው በረከት ስሞን እንዴት የሚጠላውን አማራ ሊያስብለት ይችላል?
የእድሜውን ከግማሽ በላይ ሀረር እና ትግራይ ውስጥ ሲርመጠመጥ ያሳለፈው እና ትግሪኛ ተናጋሪው አዲሱ ለገሰ በምንም ተአምር ለአማራ ሊቆረቆር ይችላል?
ትግሬው ህላዊ ዮሴፍ እንደት ለአማራ ሊጨነቅ ይችላል?
የትግሬን የአምባሻ ዱቄት ተሸከም ቢሉት የማያቅማማው ሎሌ ደመቀ መኮንን እንደት አማራን ሊወክል ይችላል?

የአማራ ህዝብ ብአዴን ወልቃይት እና ሌሎች በማን አለብኝነት የተወሰዱ የአማራ መሬቶች ማስመለስ እንደማይችል አሳምሮ ያውቀዋል። ማስመለስ ቢችልማ መጀመሪያውን እንዴት አሳልፎ ይሰጥ ነበር?

አዲሱ ለገሰ የተባለው የህውሃት ሎሌ በወልቃይት ጉዳይ ላይ ባደረገው ኢንተርቪው ሳያስበው አንድ እውነት አምልጦታል ። Smart ብትሆኑ ኖሮ የሰውየው ንግግር ሊያሳዝናችሁ እንጅ ሊያስፈነጥዛችሁ ባልተገባ ነበር ። ሎሌ አዲሱ ለገሰ ምን አለ ? ” የወልቃይት ጉዳይን የብአዴን ጥያቄ አይደለም አለ ።” እውነቱን ነው ። ከመነሻውም የወልቃይት ጥያቄ የ 40 ሚሊዮን የአማራ ወልቃይት ህዝብ ጥያቄ እንጂ ብአዴን የተባለው ድርጅት ጥያቄ አልነበረም ። የአማራ ህዝብ እኮ እየታጋለ ያለው ህውሃትን ብቻ ሳይሆን አማርኛ ተናጋሪ የህውሃት ክንፍ የሆነውን ብአዴንንም ጭምር ነው ።

ባለፉት 25 አመታት የወልቃይት ህዝብ እያለ ያለው ጨዋታው በየብሄርህ ከሆነ እኛን ለምን ከብሄራችን ትነጥሉናላችሁ ነው። ይሄ ደግሞ መብታቸው ነው። ቋንቋቸውን ባህላቸውን ለመጠበቅ ወደ ክልላቸው መመለስ አለባቸው።
የወያኔ አስተዳደር ስምምነት ይሄው ስለሆነ የወልቃይት ህዝብ ማንነቱን ከመሬቱ ጋር ኣያይዞ እየጠየቀ ስለሆነ መመለስ አለበት።
ዘረኛው ወያኔ አልተረዳውም እንጂ የትግራይ ህዝብ ድንበሩ ተከዜም ወልቃይትም አልነበረመም። ድንበሩ ከኢሉባቦር እስከ ኦጋዴን እስከ ሞያሌ እስከ ባድመ ነው። ነገር ግን ወያኔ የዘር ጨዋታውን ፊሽካ በማስነፋት ስለጀመረው በስግብግብነት እንደ አሳማ ከጎንደር እና ከወሎ የዋጠውን መሬት ማንቁርቱን ተይዞ መትፋቱ አይቀርም ። በመጀመሪያ በዚህ ጉዳይ ላይ ወደ ስምምነት መምጣት አለባት። ሁላችን ወሰናችን ይሄ መሆኑን መስማማት አለብን። አለበለዚያ ወያኔ በአንድ በኩል የቋንቋ መንግስት አምሮት በሌላ በኩል ደግሞ ትንሽ ለም መሬት ሲያይ ከቤንሻንጉልም ከአማራም ቦጨቅ ማድረግ እያማረው ኣይሆንም። ትክክልም አይደለም።

በብዙ መልኩ ስንገመግመው የትግሬ ወያኔ ባህሪ የክረምት ጅብ አይነት ነው ።
በአንድ በኩል በትግሬ ውስጥ ያሉ ሃብቶችን የኢፈርትንም ጭምር ፣ተፈጥሮ ሃብቱንም የኛ የትግራይ ህዝብ ብቻ ነው ይልና በአንድ እጁ ይዞ ይታያል። ንብረትነቱ የኛ ብቻ ነው ይላል። በሌላ በኩል ደግሞ የአባይን ወንዝ ፣ የጣናን ተፋሰስ እና ለም መሬት ፣ የጉጂዎችን ወርቅ ፣የጅማውን ቡና የሁላችን በማለት አብሮ ይበላል። የሌላውን በአንድ ገበታ አርገን እንብላ ይልህና የራሱን ብቻውን ይውጣል ። የራሱን በጁ ይዞ እያደለበ የሌላውን ያጫርሳል። ይሄ ጥሩ አይደለም። ለሃቹ ለሃገራችን ኣይበጅም። ብንገነጠልም እንኳን ለጉርብትና አይሆነንም። ታሪካዊ እሴቱም ጥሩ ኣይደለም።

የአማራ ህዝብም ሆነ የሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ባለፉት ወራቶች ጥያቄውን በግልፅ አስቀምጧል፡፡ ይህም ከተከዜ ማዶ ያለን ቦታ ለጎንደር መመለስን ጨምሮ የህወሃትን የበላይነት፣ ጣልቃ ገብነትና ዝርፊያ ጨርሶ መቆምንም ይጨምራል፡፡ ይህን በመናቅ ግን ጥያቄውን ሳይመልሱ መቅረት በጉልበት መሞከር ሁኔታውን የሚያብስ ሲሆን በሚሊዮን የሚቆጠር ሀይል እንኳ ቢኖራቸሁ ህዝብን ማሸነፍ እንኳን በእውን በህልማችሁ እንኳን ሊሳካላቸውሁ የማይችል ጉዳይ ነው፡፡ ይህ ዘመን እንዳለፉት 25 አመታት አይደለም። አማራ አሁን ከልሂቅ እስከ ደቂቅ ሁሉንም ያውቃል ። ወቅቱ እጅግ የተለየና ለህዝብ ምቹ የሆነ ሲሆን የፈለገውን ያህል አጋዚ ያሰማራ በመጨረሻ ላይ ግን ዘመኑ የወያኔን ፍፃሜ ማብሰሪያ ዘመን የሚሆን ነው፡፡

ወያኔ እና መሰሎቹ አንድ መገንዘብ ያለባቸው ነገር አለ ። ጥያቄዎች በሰላም መንገድ ካልተፈቱ ስንፋጅና ስንጎዳዳ ኖረን ወያኔ በጉልበት እንደወሰደው ሁሉ ከነወለዱ በጉልበት ይመለሳል ።

ማጠቃለያ
የአማራ ህዝብ ምን ማድረግ አለበት?

1~ የአማራ ህዝብ በታሪክ ታይቶ በማያውቅ ሁኔታ የተጋረጠበትን ችግር ለመፍታት እርስ በእርስ መረጃ እየተለዋወጡ በወንድማማችነት መንፈስ መደራጀት ያስፈልጋል ።አማራ በማንም እንዳይጠቃ እርስ በርስ እየተጠባበቁና እየተከላከሉ ወንድማማችነትን ማዳበር ።

2~ የገበሬውን ነገር አደራ፡፡ ከማንኛውም ጊዜ በበለጠ ሁኔታ በመረጃ እያጠነከሩ በስራው መበርታት ይኖርብታል፡፡
ዛሬ ካልተሰራና ነገ ካልተመረተ ከነገ ወዲያ ችግር ሲፈጠር ህወሃት በእርዳታ መልክ የፖለቲካም ሆነ የኢኮኖሚ ጥገኛ ለማድረግ እንዳትችል ዛሬውኑ ሁሉም በእጃችን ያለና የሚቻል ስለሆነ ሁሉም በያለበት በስራ መበርታት አለበት፡፡ በስራ የሚበረታና ራሱን የሚችል ህዝብ ምን ጊዜም አሸናፊ መሆኑ ታወቆ አርሶ አደሩ በስራው እንድበረታ መርዳት ።

3 ~ሌላው ቁልፍ ነጥብ የአማራ ቲቪ እንደ OMN መቁዋቋም አለበት።
አባቶቻችን ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው ያሉት ትልቅ ስትራቴጂ ነው ።”ህዝቤ እውቀት በማጣት ጠፋ” ይላል ነብዩ ሆሴ።ያማራ ህዝብ የጠፋው እውቀት፣መረጃ፣ በማጣቱ ነው።መረጃ የደምስር ነው።መረጃ የሌለው ማህበረሰብና ከባህር እንደ ወጣ አሳ መጨረሻቸው “ሞት” ነው ። አማራ ለህዝቡ መረጃ የሚሰጠው የራሱ የሆነ ሚዲያ እንደሚያስፈልግ ታውቆ ለተግባራዊነቱ ጥረት ማድረግ ።
ልብ ያለው ልብ ይበል!

Friday, March 10, 2017

በደብረታቦር ከተማ የህወሓት ወታደሮች ተገድለው ተገኙ | ሕወሓት በከተማዋ የጦር መሳሪያ ገፈፋ ሲያደርግ ዋለ. ከናትናኤል መኮንን ደብረታቦር ከተማ

ደብረታቦር ከተማ
ከናትናኤል መኮንን
በደቡብ ጎንደር ዞን ደብረታቦር ከተማ ቀበሌ 02 ልዩ ስሙ ወይብላ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ (ወይብላ ማርያም ቤተክርስቲያን አካባቢ) ከእስር ቤቱ ጀርባ ሁለት ወታደሮች ተገለው ተገኝተዋል ።በማንና እንዴት እንደተገደሉ ሊታወቅ ባይችልም በወታደሩ ውስጥ የነገሰው እርስ በርስ አለመተማመን ለግድያው ቀራቢ ምክንያት ሁኗል።
ወታደሮቹ ተገለው መገኘታቸውን ተከትሎ የካቲት 30 ለመጋቢት 1 /2009 ዓ.ም አጥቢያ ጀምሮ በከተማዋ የሚገኝ በህጋዊ ፍቃድ ያስመዘገቡ ታጣቂወች ጨምሮ ቤት ለቤት ገፈፉ ተጀምሯል። በቴወድሮስ አደባባይ ከቴሌው አጠገብ የሚገኘው አዳራሽ ውስጥ የሚኖሩት ወታደሮች በተለያየ የከተመዋ አቅጣጫ ለፍተሻ ተሰማርተዋል።
በድንገተኛው የመሳሪያ ገፈፉ በቀበሌ 04 ቀበሌ ውስጥ 4 በህጋዊ ፈቃድ ያስመዘገቡ ነዋሪወች መሳሪያ መገፈፉቸው ታውቋል

ዶክተር መረራ የዋስ መብታቸው እንደተከለከለ ሲገለጽላቸው በፍርድ ቤት ይህን ተናገሩ

ዶክተር መረራ የዋስ መብታቸው እንደተከለከለ ሲገለጽላቸው በፍርድ ቤት ይህን ተናገሩ:-
“ 1) ከእነጄኔራል መንግስቱ ንዋይና ጄኔራል ታደሰ ብሩ ዘመን ጀምሮ ከአንድ ትውልድ በላይ ገዳዮችና ሟቾች አሳሪዎችና ታሳሪዎች በበዛበት የሀገራችን የፖለቲካ ድራማ ውስጥ በመቆየት አንድ አንድ ከሆዱ በላይ ለሀገሩ የሚያስብ ምሁር ማድረግ እንዳለበት ሁሉ ከአርባ አምስት አመታት በላይ ለሀገሬ የተሻለ ለውጥ እንዲመጣ በታማኝነት መታገሌ እየታወቀ ወደ ጎን መገፋቱ፡-
2) ለሁላችንም የምትሆንና በእኩልነት የምታስተናግደን ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ እንድትፈጠርና ነፃ የፍትህ ሥርዓት በሀገራችን እንዲሰፍን ላለፉት ሃያ አምስት አመታት በመታገሌ መከሰሴ አንሶ የአገሪቱ ፓርላማ አባል የነበርኩ ሰው ለተራ ወንጀለኛ የሚፈቀድ የዋስ መብት በመከልከሌ የተሰማኝ ጥልቅ ሀዘን ለራሴ ብቻ ሳይሆን እኛም ሆን ልጆቻችን በሰላም ይኖሩበታል ለምንለው መከረኛ ሀገራችንና አላልፍለት ብሎ ስታመስ ለሚኖር መከረኛ ሕዝባችን ጭምር መሆኑን እንዲታወቅልኝ ነው፡፡







Wednesday, March 8, 2017

እስከመቼ ሃይለማሪያም በነሳሞራ እየተናቀ ይኖራል ? #ግርማ_ካሳ


የአፍሪካ ኢንተሊጀንስ ጠቅሶ ዘሃበሻ የሚከትለዉን ዘግቧል። አፍሪአ ኢንተሊጄንስ የሚታመን ምንጭ ነው። ኢሕአዴእግ ስልጣን እንደያዘ ገና የአዲስ አበባ ቻርተር ሳይጸድቅ የኢትዮጵያ አወቃቀር ምን እንደምትመስል አፍሪካ ኢንተሊጀንስ ነበር ያወጣው። ብዙም አልቆይም በቻርተሩ ጸደቀ።
 
ይሄ ሜዲያ ብዙዎቻችን ለአንባቢያን ለምሳየት ስንሞክር የነበረውን ነገር ነው በግልጽ ያስቀመጠው። በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለው ሁለት መንግስት ነው። አንደኛው በሃይለማሪያም ደሳለኝ የሚመራው ሲሆን፣ ሁለተኛ በጥቂት ህወሃቶች የሚመራውው፣ ደህንነቱን እና ሰርራዊቱን የሚቆጣጠረውው፣ እነ ኃይለማሪያም የማይታዘዝ ብቻ ሳይሆንን የሚንቅንና መመሪያዎች በጎን እየላከ ዉሳኔያቸውን የሚሰርዝ አካል ነው።
 
እና ሃይለማሪያም የአገር ችግር በድርድር እንዲፈታ ያለው ፖለቲካ እንዲለዝብ የሕዝብ ጥያቄ እንዲፌታ ይፈልግጋሉ። ይህ አሁኡንን ይደረጋል የተባለውንን ድርድር ያመቻቹት እነርሱ ናቸው። ግን የሕወሃቱ ሁለተኛው መንግስት ድርድር የሚባል ነገር አይፈለግም። እያሰረ፣ እየገድደለ፣ እያፈናቀል በጥጋብና በ እርብሪት መግዛት ነው የሚፈለገው። ለዚህ ነው ተቃዋምሚዎች ከድርድሩ እዲወጡ አመራሮችን እያሰረ ያለውና የሚከሰው።
 
ህወሃት ለ547 መቀመጫ 38 ብቻ ነው ድምጽ ያለው። በኢሕአዴግ ዉስጥ ደግሞ አንድ አራተኛ ብቻ ነው መቀመጫ ያለው። ታዲያ እንዴት በዚህ መልክ እየተዋረዱና መሳቂያ እየሆኑ ዝም ብለው ያያሉ ? እስከ መቼ ነው እነዚህ የታሪክ አተላዎችን ይታገሳሉ ? እስከመቼ ነው፣ ግድ የለም ለሌላው አይቁሞ ለራሳቸውና ለክብራቸው እንኳን የማይቆሙት ? እስከ መቼ እነ ሶሞራ እንደ ዉሻ እያዩዋቸው ዝም የሚሉት ?
 
አንድ ጊዜ በብአዴን ጉባዬ አባላቱ “እነርሱ ባልፎቅ ሲሆኑ እኛ ሎተሪ ሻጮች ነው የሆንነው” እያሉ ሲያማረርሩ ነበር። እስከመቼ ነው የሚያማርሩት ?

ዓላማውን ለሳተ ድርድር ከዚህ በላይ መንፈራገጥ ትርፉ ትዝብት ነው !!! by yidinekachew kebede

ዓላማውን ለሳተ ድርድር ከዚህ በላይ መንፈራገጥ ትርፉ ትዝብት ነው !!! yidinekachew kebede
—— ” ዋንኛ ዓላማ አድርገው የተስማሙበት ፣ የህዝብን ጥያቄ የቱንም ያህል ምላሽ የማይሰጥ ከመሆኑ ባለፈ ለአገዛዙ ሥርዓት መደላድል የሚፈጥር ነው።” ——– “አገር በድርድር ነው የሚገነባው” ለመባሉ ፋይዳው ፈርጀ ብዙ ነው። አገራችን ኢትዮጵያ አሁን ላይ ከፍተኛ የሆነ ፓለቲካ ቀውስ ውስጥ ትገኛለች ። የቀውሱ መንስኤ ከበፊት ጀምሮ የመጣ ምስቅልቅሉ የወጣ የ 26 ዓመተ ፣ የከፋፍለህ ግዛ በተኛ የአገር አንድነት ፓሊሲ መሆኑ ብዙም አስረጂ አያስፈልገውም ።ይህም በመሆኑ እሱን ተከትሎ የመጣው ማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እና የህወሃት/ኢህአዴግ ደካማ አስተዳደራዊ ሥርዓት ጭምር ነው። እንዲህ አይነቱ ሥርዓት ያንገፈገፈው እና በምላሹ አስተዳድርሃለው ለሚለው አካል ቁጣውን በቻለው ሃቅም ገልፆ፤ ለቁጣው ትዕግስትን ተላብሶ በአሰተዋይነት እና በንቃት የሚሆነውን ምላሽ እየተከታተለ ይገኛል። ይህን በገደምዳሜ ቢሆንም የተረዳው፣ የአገዛዙ ሥርዓት ከሚመጣበት ህዝባዊ መሃበል እራሱን ለመሸሸግ እና እድሜውን ለማራዘም ደፋ ቀና እያለ ይገኛል። ይሁን እንጂ እንደራደራለን ወይም ለመደራደር ዝግጁ ነን በማለት ከአገዛዙ ሥርዓት ጋር በእኩሉ የሚታዩት፣በድርድሩ ላይ የአገዛዙ ሥርዓት ያህል እንኳን ባይሆንም በተረዱበት ልክ ሲጨነቁበት አለማያት ( ለእነሱ የተጨነቁበት)ለመሰላቸው የመጀመሪያው ትዝብት ነው። – በመሰረቱ ከዛሬ ስድስት ወር በፊት፣ አገራችን ከገባችብት ፓለቲካዊ ቀውስ እና እሱን ተከትሎ ለተፈጠረው ችግር በዘለቄታዊነት መፍትሔ ሊመጣ የሚችለው ፤ ገደብ ሳይበጅለት በአገር ውስጥ እና በውጪ ሁሉን አቀፍ ውይይትና ድርድር ሲካሄድ ብቻ ነው ! የሚል እምነት እንዳለኝ መጠነኛ አመላካች የሆነ ሃሳቤን በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ ገልጪ ነበር። የሚገርመው ነገር ጋዜጣው ላይ የወጣውን ጽሁፍ ሳላነበው፣ ለሁለት ወር ያህል ለእስራት ብዳርግም። ምን ይሄ ብቻ የአስቸኳይ አዋጅ ጥሰሃል ተብዬ ከቀረበብኝ መጠይቅ ውስጥ አንዱ መሆኑ እንጂ፣ ምን አልባትም ይሄ ጽሁፍ ለንባብ ከበቃ በኋል እስሩም ሆነ ሌላው ነገር መምጫው መንገድ አይታወቅም እና የሚሆነውን መጠበቅ የተሻለ ነው። ግን ይሄም ቢሆን እንደ ትላንትናው ዛሬም ለአገሬ ቀናውን በማሰብ ነውና ለራሴ ክፉ አልመኝም። ወደ ተነሳሁበት ጉዳይ ስመለስ ፣ የአገዛዙ ሥርዓት ወዶ ሳይሆን በግዴታ ፣ በህዝባዊ ተቃውሞ አማካኝነት እዚህም እዚያ ተፍ ተፍ እያለ ይገኛል። ለዚህም በኦሮሚያ ፣ በዐማራ እንዲሁም በደቡብ አንድ አንድ አካባቢዎች የተነሳው ህዝባዊ ተቃውሞና አመጽ እንዲሁም እሱን ተከትሎ የተከፈለው የህይወት መሰዋዕትነት እና እስር እንዲሁም እንግልት ጭምር ነው። ይህም በታሪክ ተመዝግቦ ወደፊት የሚዘከር ነው። የአገዛዙ ሥርዓት ከፓርቲዎች ጋር ድርድር እና ውይይት አካሂዷል ማለቱን መሠረት በማድረግ፣ ዘላቂ የሆነ ችግር ፈቺ አማራጭ ሃሳባችን በሠነድ በማዘጋጀት ፣ የድርድሩ ዋና ዓላማ ፤ ብሔራዊ እርቅ በመፍጠር የፓለቲካ እና የህሊና እስረኞችን በመፍታት፣ በአገር ውስጥ እንዲሁም ከአገር ውጪ የሚገኙ የፓለቲካ ሃይሎች ጠመንጃ ያነገብ ጭምር የሚሳተፉበት ሆኖ ፤ ህዝብን የስልጣን ባለቤት መሆኑን ታሳቢ በማድረግ፣ ሁሉን አቀፍ ውይይት በማካሄድ ወጤት ማምጣት ከተቻለ በሚል ቀና ሃሳብ ድርድሩን እና ውይይቱን ደግፊ ነበር ። ይሁን እንጂ በድርድሩ ቅድመ ሁኔታ እና በድርድሩ ሊመለሱ የሚገባቸው ፣ ከምንም በላይ ድርድሩ ለአገራችን ዘላቂ የሆነ መፍትሔ እንዲያስገኝ ከመሻት ይልቅ በተወሰኑ ፓርቲዎች ለዛውም ህዝባዊ ተቀባይነታቸው አሻሚ የሆኑ ፣ በገደምዳሜው ቢሆንም የህዝብ ድጋፍ ያላቸው በቁጥር ከሦስት የማይበልጡ ፓርቲዎች ፤ሊሻሻሉ ወይም ሊለወጡና ሊጨመሩ የሚችሉ የህግ ማዕቀፎች እና የመድበለ ፓርቲ ተሳትፎ እና መጪውን የምርጫ ወቅት ዓላማ በማድረግ፤ ለመደራደር በድርድር ሥነ-ስርዓት ላይ ዋንኛ ዓላማ አድርገው መክረው መስማማታቸው፣ ተገልፆል ።ይህ ደግሞ የተለመደው የአዙሪት ገደል ውስጥ እልም ብሎ የሚያስገባ መሆኑን ለመገንዘብ ብዙም አዳጋች አይደለም ። ይህም በመሆኑ እንደራደራለን ወይም እንከራከራለን ምን አልባትም እንወያያለን ለሚሉ ከዚህ በላይ መዳከር ተጨማሪ ትዝብት ውስጥ የሚጥላቸው ካልሆነ በስተቀር ትርፉ ፖለቲካዊ ኪሣራ ነው ። – በዚህ መሰረት ዋንኛ ዓላማ አድርገው የተስማሙበት ፣የህዝብን ጥያቄ የቱንም ያህል ምላሽ የማይሰጥ ከመሆኑ ባለፈ ለአገዛዙ ሥርዓት መደላድል የሚፈጥር ነው። ሥርዓቱም ቀደም ብሎ ይህንን አምኖ በግልጽ ፤ በፓርላማ መክፈቻ ላይ ፕሬዝዳንቱ ፣ ጉድለታችን ነው ! ልናሻሽለው ይገባል ያሉትን ዋና ዓላማ በማድረግ ፣ እንደራደራለን ብለው በተቃዋሚ ጎራ የተሰለፉት ሳይሸራረፍ እንደ ወረደ ዓላማቸው አድርገው መቀበላቸው፤ ለህወሓት/ኢህአዴግ ትልቅ ድል ነው። ከዚህ በኋል እዳው ገብስ ነው። ምክንያቱም ለአገዛዙ ምቹ የሆነ የድርድር ዓላማ ተቀምጧል ። መቼም ቢሆን በይትም ቦታ፣ ዋና ዓላማን ያልሳተ ንዑስ ዓላማ እና ይሄን መሰረት ያደረገ የመወያያ አጀንዳ መኖሩ ሣይንሳዊ እውነት ነው። ይህ እውነታ የድርድሩን ዋና ዓላማ ፈጽሞ የሚቀይረው አይደለም። ከረፈደም ቢሆን ይሄን ለማወቅ የሞከሩ አንዳንዶቹ፣ በድርድሩ አጀንዳ ላይ በዋና ዓላማ ላይ ያላስቀመጥናቸውን ሃሳቦች አንስተን እንደራደራለን ይላሉ፣ ይሄ ደግሞ የፖለቲካ ጥበብ ወይም የድርድር መሠረታዊ መርሆዎች ላይ የሚኖራቸው ግንዛቤ ብልጥጥ አድርጎ ለህዝብ አጋልጦ የሚሰጥ ተጨማሪ ትዝብ ነው። – ምን ይሄ ብቻ ! የድርድሩ ዓላማ አጥጋቢ ውጤት ለሌለው ነገር። ስንደራደር ማን ይታዘበን ፣ እነማንስ መሀል ሆነው ያደራድሩን ፤ በሚል ጠንካራ ክርክር እንደሚደረግ ተደራዳሪዎች በአንድም ይሁን በሌላ መንገድ እየገለፁ ይገኛሉ። እዚህ ላይ እኔን ያስቀኛል! እንዳሁም የህወሓት/የኢህአዴግ ብልጠት የተሞላባት ጨዋታ የተጫወተው እዚህ ላይ ነው። ገዠው መንግሥት የሚፈልገውን የድርድሩ ዋና አላማ ቀድሞ ማኖ ካስነካ በኋላ፤ አደራዳሪ እና ታዛቢ ቀጥሎ እንዲሆን አስደረገ፣ እሱ በሚመቸው ነገር ላይ ማንስ ቢመጣ ምን ቸገረው። በድርድሩ ከተቃዋሚ በላይ መንግሥት እየሰራ ነው መባሉ ለምን ሆነና ?! ይህም በመሆኑ ተቃዋሚዎች የሚጠቁማቸውን ታዛቢ እና አደራዳሪ ለህዝብ ግንኙነት ሥራ እንዲረዳ የውሸት መንገጫገጭ ያሳያል ፣ ምን አልባት ሙሉ ለሙሉ ወይም ከ 75 በፐርሰንት በላይ ሊቀበል ይችላል። በዚህን ጊዜ ተቀዋሚዎች የድል ከበሮ ይደልቁ ይሆናል። ነገር ግን ለአገራቸው ቀናውን በማሰብ ፣ በአደራዳሪነት ውይም በታዛቢነት ለማገልገል ፍላጎት ያላቸው ይኖሩ ይሆናል። ግን የዚህን ጉድ በዚህ ደራጃ መሆኑ ሲገባቸው ፣ ቀኝ ወደ-ኋላ ማለታቸው አይቀሬ ነው። ይሄም ሌላኛው ትዝብት ነው። – ይዚህ ጽሁፍ አንባቢያን ፣ ከላይ የገለፅኩት በአብዛኛው ፣ በዚህ ድርድር ላይ ፍላጎት ላላቸው ገና ከጅምሩ ፣ይሄን ሃሳቤን ለማጋራት በቻልኩት አቅም ሁሉ ሞክሪያለው። ይታይ የነበረ ስእተት ወቅቱን ጠብቆ በገባኝ መጠን እርማት እንዲደረግበት ጥረት አድርጊያለው ። ከዛሬ ነገ የሚሻል ነገር ካለ ብዬ ለመታገሥ ለራሴ እድል ሰጥቻለው። ይሁን እንጂ በእኛ ሰፈር የአራዳ ቋንቋ ( ወፍ የለም)። ስለዚህም ዓላማውን ለሳተ ድርድር ከዚህ በላይ መንፈራገጥ ትርፉ ትዝብት ነው !!! በማላት የዚህ ጽሁፍ ማብቂያ ይሄ ይሁን፣ ለሌላው ደግሞ በሌላ ቀን ። አንባቢያን ከአክብሮት ጋር የምጠይቀው ይህ የግል ሃሳቤ እንጂ የይትኛው ፓርቲ አቋም የሚመለከት አይደለም።(ይድነቃቸው ከበደ) – ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !!!

ወያኔ የዩንቨርሲቲ መምህራንና ሠራተኞችን ጥልቅ ተሃድሶ በሚል ስብሰባ ጠምዶ ይዟል፤ muluken tesfaw

ወያኔ የዩንቨርሲቲ መምህራንና ሠራተኞችን ጥልቅ ተሃድሶ በሚል ስብሰባ ጠምዶ ይዟል፤
muluken tesfaw . የትግሬ ወያኔ መንግሥት በሁሉም ዩንቨርሲቲዎች ያሉ መምህራንና ሠራተኞችን ጥልቅ ተሃድሶ በሚል ስብሰባ ጠምዶ እንደያዛቸው ከየዩንቨርሲቲዎቹ የሚወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ከወሎና ከዓለማያ ዩንቨርሲቲዎች የደረሱን መረጃዎች እንደሚያመለክቱት መንግሥት የሕዝብን ጥያቄ የመልካም አስተዳደርና የተገልጋዩ ሕብረተሰብ ውጣ ውረድ መማረር ነው በሚል ለሚዲያ ሽፋን ለመስጠት ደፋ ቀና እያለ ነው ብለዋል፡፡
ምሁራኑ እንደሚሉት ጥልቅ ተሃድሶ በሚል ለመገምገሚያ በቀረበው ሰነድ መሠረት በሕዝብ የተጠየቁ ጥያቄዎች ቦታ አልተሰጣቸውም ተብሏል፤ ‹‹ይልቁንም በመልካም አስተዳደር እጦት በሚል እየጠሸፈኑ ነው›› ሲሉ ተችተዋል፡፡
በወሎ ዩንቨርሲቲ በሁለቱም ግቢዎች ያሉ መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች በስብሰባው ‹‹ከሕዝብ ጋር የመታረቅ ፍላጎት የሌለው መንግሥት›› ሲሉ ተችተዋል፡፡ በዓለማያ ዩንቨርሲቲ አፍረንቀሎ አዳራሽ መምህራን፣ በኦዲተሪየም ወይም አሮጌው አዳራሽ የአስተዳደር ሠራተኞች እንዲሁም በሴቶች ላይብራሪ ደግሞ የጽዳትና የጥበቃ ሠራተኞች ከትላንት ጀምሮ ስብሰባ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የዐማራ ተወላጅ መምህራን በዘራቸው ምክንያት እየደረሰባቸው ያለውን በደል አንስተዋል ተብሏል፡፡
ምሁራኑ በውጭ በነጻነት የሚኖሩ ምሁራን አስተያየታቸውን ይሰጡበት ዘንድ የተሃድሶ ሰነድ የተባለውን ዶክመት አብረው የላኩ ሲሆን ከፊሉ ከዚህ ዜና ጋር አብሮ ተያይዟል፡፡