Friday, March 10, 2017

በደብረታቦር ከተማ የህወሓት ወታደሮች ተገድለው ተገኙ | ሕወሓት በከተማዋ የጦር መሳሪያ ገፈፋ ሲያደርግ ዋለ. ከናትናኤል መኮንን ደብረታቦር ከተማ

ደብረታቦር ከተማ
ከናትናኤል መኮንን
በደቡብ ጎንደር ዞን ደብረታቦር ከተማ ቀበሌ 02 ልዩ ስሙ ወይብላ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ (ወይብላ ማርያም ቤተክርስቲያን አካባቢ) ከእስር ቤቱ ጀርባ ሁለት ወታደሮች ተገለው ተገኝተዋል ።በማንና እንዴት እንደተገደሉ ሊታወቅ ባይችልም በወታደሩ ውስጥ የነገሰው እርስ በርስ አለመተማመን ለግድያው ቀራቢ ምክንያት ሁኗል።
ወታደሮቹ ተገለው መገኘታቸውን ተከትሎ የካቲት 30 ለመጋቢት 1 /2009 ዓ.ም አጥቢያ ጀምሮ በከተማዋ የሚገኝ በህጋዊ ፍቃድ ያስመዘገቡ ታጣቂወች ጨምሮ ቤት ለቤት ገፈፉ ተጀምሯል። በቴወድሮስ አደባባይ ከቴሌው አጠገብ የሚገኘው አዳራሽ ውስጥ የሚኖሩት ወታደሮች በተለያየ የከተመዋ አቅጣጫ ለፍተሻ ተሰማርተዋል።
በድንገተኛው የመሳሪያ ገፈፉ በቀበሌ 04 ቀበሌ ውስጥ 4 በህጋዊ ፈቃድ ያስመዘገቡ ነዋሪወች መሳሪያ መገፈፉቸው ታውቋል

ዶክተር መረራ የዋስ መብታቸው እንደተከለከለ ሲገለጽላቸው በፍርድ ቤት ይህን ተናገሩ

ዶክተር መረራ የዋስ መብታቸው እንደተከለከለ ሲገለጽላቸው በፍርድ ቤት ይህን ተናገሩ:-
“ 1) ከእነጄኔራል መንግስቱ ንዋይና ጄኔራል ታደሰ ብሩ ዘመን ጀምሮ ከአንድ ትውልድ በላይ ገዳዮችና ሟቾች አሳሪዎችና ታሳሪዎች በበዛበት የሀገራችን የፖለቲካ ድራማ ውስጥ በመቆየት አንድ አንድ ከሆዱ በላይ ለሀገሩ የሚያስብ ምሁር ማድረግ እንዳለበት ሁሉ ከአርባ አምስት አመታት በላይ ለሀገሬ የተሻለ ለውጥ እንዲመጣ በታማኝነት መታገሌ እየታወቀ ወደ ጎን መገፋቱ፡-
2) ለሁላችንም የምትሆንና በእኩልነት የምታስተናግደን ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ እንድትፈጠርና ነፃ የፍትህ ሥርዓት በሀገራችን እንዲሰፍን ላለፉት ሃያ አምስት አመታት በመታገሌ መከሰሴ አንሶ የአገሪቱ ፓርላማ አባል የነበርኩ ሰው ለተራ ወንጀለኛ የሚፈቀድ የዋስ መብት በመከልከሌ የተሰማኝ ጥልቅ ሀዘን ለራሴ ብቻ ሳይሆን እኛም ሆን ልጆቻችን በሰላም ይኖሩበታል ለምንለው መከረኛ ሀገራችንና አላልፍለት ብሎ ስታመስ ለሚኖር መከረኛ ሕዝባችን ጭምር መሆኑን እንዲታወቅልኝ ነው፡፡







Wednesday, March 8, 2017

እስከመቼ ሃይለማሪያም በነሳሞራ እየተናቀ ይኖራል ? #ግርማ_ካሳ


የአፍሪካ ኢንተሊጀንስ ጠቅሶ ዘሃበሻ የሚከትለዉን ዘግቧል። አፍሪአ ኢንተሊጄንስ የሚታመን ምንጭ ነው። ኢሕአዴእግ ስልጣን እንደያዘ ገና የአዲስ አበባ ቻርተር ሳይጸድቅ የኢትዮጵያ አወቃቀር ምን እንደምትመስል አፍሪካ ኢንተሊጀንስ ነበር ያወጣው። ብዙም አልቆይም በቻርተሩ ጸደቀ።
 
ይሄ ሜዲያ ብዙዎቻችን ለአንባቢያን ለምሳየት ስንሞክር የነበረውን ነገር ነው በግልጽ ያስቀመጠው። በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለው ሁለት መንግስት ነው። አንደኛው በሃይለማሪያም ደሳለኝ የሚመራው ሲሆን፣ ሁለተኛ በጥቂት ህወሃቶች የሚመራውው፣ ደህንነቱን እና ሰርራዊቱን የሚቆጣጠረውው፣ እነ ኃይለማሪያም የማይታዘዝ ብቻ ሳይሆንን የሚንቅንና መመሪያዎች በጎን እየላከ ዉሳኔያቸውን የሚሰርዝ አካል ነው።
 
እና ሃይለማሪያም የአገር ችግር በድርድር እንዲፈታ ያለው ፖለቲካ እንዲለዝብ የሕዝብ ጥያቄ እንዲፌታ ይፈልግጋሉ። ይህ አሁኡንን ይደረጋል የተባለውንን ድርድር ያመቻቹት እነርሱ ናቸው። ግን የሕወሃቱ ሁለተኛው መንግስት ድርድር የሚባል ነገር አይፈለግም። እያሰረ፣ እየገድደለ፣ እያፈናቀል በጥጋብና በ እርብሪት መግዛት ነው የሚፈለገው። ለዚህ ነው ተቃዋምሚዎች ከድርድሩ እዲወጡ አመራሮችን እያሰረ ያለውና የሚከሰው።
 
ህወሃት ለ547 መቀመጫ 38 ብቻ ነው ድምጽ ያለው። በኢሕአዴግ ዉስጥ ደግሞ አንድ አራተኛ ብቻ ነው መቀመጫ ያለው። ታዲያ እንዴት በዚህ መልክ እየተዋረዱና መሳቂያ እየሆኑ ዝም ብለው ያያሉ ? እስከ መቼ ነው እነዚህ የታሪክ አተላዎችን ይታገሳሉ ? እስከመቼ ነው፣ ግድ የለም ለሌላው አይቁሞ ለራሳቸውና ለክብራቸው እንኳን የማይቆሙት ? እስከ መቼ እነ ሶሞራ እንደ ዉሻ እያዩዋቸው ዝም የሚሉት ?
 
አንድ ጊዜ በብአዴን ጉባዬ አባላቱ “እነርሱ ባልፎቅ ሲሆኑ እኛ ሎተሪ ሻጮች ነው የሆንነው” እያሉ ሲያማረርሩ ነበር። እስከመቼ ነው የሚያማርሩት ?

ዓላማውን ለሳተ ድርድር ከዚህ በላይ መንፈራገጥ ትርፉ ትዝብት ነው !!! by yidinekachew kebede

ዓላማውን ለሳተ ድርድር ከዚህ በላይ መንፈራገጥ ትርፉ ትዝብት ነው !!! yidinekachew kebede
—— ” ዋንኛ ዓላማ አድርገው የተስማሙበት ፣ የህዝብን ጥያቄ የቱንም ያህል ምላሽ የማይሰጥ ከመሆኑ ባለፈ ለአገዛዙ ሥርዓት መደላድል የሚፈጥር ነው።” ——– “አገር በድርድር ነው የሚገነባው” ለመባሉ ፋይዳው ፈርጀ ብዙ ነው። አገራችን ኢትዮጵያ አሁን ላይ ከፍተኛ የሆነ ፓለቲካ ቀውስ ውስጥ ትገኛለች ። የቀውሱ መንስኤ ከበፊት ጀምሮ የመጣ ምስቅልቅሉ የወጣ የ 26 ዓመተ ፣ የከፋፍለህ ግዛ በተኛ የአገር አንድነት ፓሊሲ መሆኑ ብዙም አስረጂ አያስፈልገውም ።ይህም በመሆኑ እሱን ተከትሎ የመጣው ማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እና የህወሃት/ኢህአዴግ ደካማ አስተዳደራዊ ሥርዓት ጭምር ነው። እንዲህ አይነቱ ሥርዓት ያንገፈገፈው እና በምላሹ አስተዳድርሃለው ለሚለው አካል ቁጣውን በቻለው ሃቅም ገልፆ፤ ለቁጣው ትዕግስትን ተላብሶ በአሰተዋይነት እና በንቃት የሚሆነውን ምላሽ እየተከታተለ ይገኛል። ይህን በገደምዳሜ ቢሆንም የተረዳው፣ የአገዛዙ ሥርዓት ከሚመጣበት ህዝባዊ መሃበል እራሱን ለመሸሸግ እና እድሜውን ለማራዘም ደፋ ቀና እያለ ይገኛል። ይሁን እንጂ እንደራደራለን ወይም ለመደራደር ዝግጁ ነን በማለት ከአገዛዙ ሥርዓት ጋር በእኩሉ የሚታዩት፣በድርድሩ ላይ የአገዛዙ ሥርዓት ያህል እንኳን ባይሆንም በተረዱበት ልክ ሲጨነቁበት አለማያት ( ለእነሱ የተጨነቁበት)ለመሰላቸው የመጀመሪያው ትዝብት ነው። – በመሰረቱ ከዛሬ ስድስት ወር በፊት፣ አገራችን ከገባችብት ፓለቲካዊ ቀውስ እና እሱን ተከትሎ ለተፈጠረው ችግር በዘለቄታዊነት መፍትሔ ሊመጣ የሚችለው ፤ ገደብ ሳይበጅለት በአገር ውስጥ እና በውጪ ሁሉን አቀፍ ውይይትና ድርድር ሲካሄድ ብቻ ነው ! የሚል እምነት እንዳለኝ መጠነኛ አመላካች የሆነ ሃሳቤን በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ ገልጪ ነበር። የሚገርመው ነገር ጋዜጣው ላይ የወጣውን ጽሁፍ ሳላነበው፣ ለሁለት ወር ያህል ለእስራት ብዳርግም። ምን ይሄ ብቻ የአስቸኳይ አዋጅ ጥሰሃል ተብዬ ከቀረበብኝ መጠይቅ ውስጥ አንዱ መሆኑ እንጂ፣ ምን አልባትም ይሄ ጽሁፍ ለንባብ ከበቃ በኋል እስሩም ሆነ ሌላው ነገር መምጫው መንገድ አይታወቅም እና የሚሆነውን መጠበቅ የተሻለ ነው። ግን ይሄም ቢሆን እንደ ትላንትናው ዛሬም ለአገሬ ቀናውን በማሰብ ነውና ለራሴ ክፉ አልመኝም። ወደ ተነሳሁበት ጉዳይ ስመለስ ፣ የአገዛዙ ሥርዓት ወዶ ሳይሆን በግዴታ ፣ በህዝባዊ ተቃውሞ አማካኝነት እዚህም እዚያ ተፍ ተፍ እያለ ይገኛል። ለዚህም በኦሮሚያ ፣ በዐማራ እንዲሁም በደቡብ አንድ አንድ አካባቢዎች የተነሳው ህዝባዊ ተቃውሞና አመጽ እንዲሁም እሱን ተከትሎ የተከፈለው የህይወት መሰዋዕትነት እና እስር እንዲሁም እንግልት ጭምር ነው። ይህም በታሪክ ተመዝግቦ ወደፊት የሚዘከር ነው። የአገዛዙ ሥርዓት ከፓርቲዎች ጋር ድርድር እና ውይይት አካሂዷል ማለቱን መሠረት በማድረግ፣ ዘላቂ የሆነ ችግር ፈቺ አማራጭ ሃሳባችን በሠነድ በማዘጋጀት ፣ የድርድሩ ዋና ዓላማ ፤ ብሔራዊ እርቅ በመፍጠር የፓለቲካ እና የህሊና እስረኞችን በመፍታት፣ በአገር ውስጥ እንዲሁም ከአገር ውጪ የሚገኙ የፓለቲካ ሃይሎች ጠመንጃ ያነገብ ጭምር የሚሳተፉበት ሆኖ ፤ ህዝብን የስልጣን ባለቤት መሆኑን ታሳቢ በማድረግ፣ ሁሉን አቀፍ ውይይት በማካሄድ ወጤት ማምጣት ከተቻለ በሚል ቀና ሃሳብ ድርድሩን እና ውይይቱን ደግፊ ነበር ። ይሁን እንጂ በድርድሩ ቅድመ ሁኔታ እና በድርድሩ ሊመለሱ የሚገባቸው ፣ ከምንም በላይ ድርድሩ ለአገራችን ዘላቂ የሆነ መፍትሔ እንዲያስገኝ ከመሻት ይልቅ በተወሰኑ ፓርቲዎች ለዛውም ህዝባዊ ተቀባይነታቸው አሻሚ የሆኑ ፣ በገደምዳሜው ቢሆንም የህዝብ ድጋፍ ያላቸው በቁጥር ከሦስት የማይበልጡ ፓርቲዎች ፤ሊሻሻሉ ወይም ሊለወጡና ሊጨመሩ የሚችሉ የህግ ማዕቀፎች እና የመድበለ ፓርቲ ተሳትፎ እና መጪውን የምርጫ ወቅት ዓላማ በማድረግ፤ ለመደራደር በድርድር ሥነ-ስርዓት ላይ ዋንኛ ዓላማ አድርገው መክረው መስማማታቸው፣ ተገልፆል ።ይህ ደግሞ የተለመደው የአዙሪት ገደል ውስጥ እልም ብሎ የሚያስገባ መሆኑን ለመገንዘብ ብዙም አዳጋች አይደለም ። ይህም በመሆኑ እንደራደራለን ወይም እንከራከራለን ምን አልባትም እንወያያለን ለሚሉ ከዚህ በላይ መዳከር ተጨማሪ ትዝብት ውስጥ የሚጥላቸው ካልሆነ በስተቀር ትርፉ ፖለቲካዊ ኪሣራ ነው ። – በዚህ መሰረት ዋንኛ ዓላማ አድርገው የተስማሙበት ፣የህዝብን ጥያቄ የቱንም ያህል ምላሽ የማይሰጥ ከመሆኑ ባለፈ ለአገዛዙ ሥርዓት መደላድል የሚፈጥር ነው። ሥርዓቱም ቀደም ብሎ ይህንን አምኖ በግልጽ ፤ በፓርላማ መክፈቻ ላይ ፕሬዝዳንቱ ፣ ጉድለታችን ነው ! ልናሻሽለው ይገባል ያሉትን ዋና ዓላማ በማድረግ ፣ እንደራደራለን ብለው በተቃዋሚ ጎራ የተሰለፉት ሳይሸራረፍ እንደ ወረደ ዓላማቸው አድርገው መቀበላቸው፤ ለህወሓት/ኢህአዴግ ትልቅ ድል ነው። ከዚህ በኋል እዳው ገብስ ነው። ምክንያቱም ለአገዛዙ ምቹ የሆነ የድርድር ዓላማ ተቀምጧል ። መቼም ቢሆን በይትም ቦታ፣ ዋና ዓላማን ያልሳተ ንዑስ ዓላማ እና ይሄን መሰረት ያደረገ የመወያያ አጀንዳ መኖሩ ሣይንሳዊ እውነት ነው። ይህ እውነታ የድርድሩን ዋና ዓላማ ፈጽሞ የሚቀይረው አይደለም። ከረፈደም ቢሆን ይሄን ለማወቅ የሞከሩ አንዳንዶቹ፣ በድርድሩ አጀንዳ ላይ በዋና ዓላማ ላይ ያላስቀመጥናቸውን ሃሳቦች አንስተን እንደራደራለን ይላሉ፣ ይሄ ደግሞ የፖለቲካ ጥበብ ወይም የድርድር መሠረታዊ መርሆዎች ላይ የሚኖራቸው ግንዛቤ ብልጥጥ አድርጎ ለህዝብ አጋልጦ የሚሰጥ ተጨማሪ ትዝብ ነው። – ምን ይሄ ብቻ ! የድርድሩ ዓላማ አጥጋቢ ውጤት ለሌለው ነገር። ስንደራደር ማን ይታዘበን ፣ እነማንስ መሀል ሆነው ያደራድሩን ፤ በሚል ጠንካራ ክርክር እንደሚደረግ ተደራዳሪዎች በአንድም ይሁን በሌላ መንገድ እየገለፁ ይገኛሉ። እዚህ ላይ እኔን ያስቀኛል! እንዳሁም የህወሓት/የኢህአዴግ ብልጠት የተሞላባት ጨዋታ የተጫወተው እዚህ ላይ ነው። ገዠው መንግሥት የሚፈልገውን የድርድሩ ዋና አላማ ቀድሞ ማኖ ካስነካ በኋላ፤ አደራዳሪ እና ታዛቢ ቀጥሎ እንዲሆን አስደረገ፣ እሱ በሚመቸው ነገር ላይ ማንስ ቢመጣ ምን ቸገረው። በድርድሩ ከተቃዋሚ በላይ መንግሥት እየሰራ ነው መባሉ ለምን ሆነና ?! ይህም በመሆኑ ተቃዋሚዎች የሚጠቁማቸውን ታዛቢ እና አደራዳሪ ለህዝብ ግንኙነት ሥራ እንዲረዳ የውሸት መንገጫገጭ ያሳያል ፣ ምን አልባት ሙሉ ለሙሉ ወይም ከ 75 በፐርሰንት በላይ ሊቀበል ይችላል። በዚህን ጊዜ ተቀዋሚዎች የድል ከበሮ ይደልቁ ይሆናል። ነገር ግን ለአገራቸው ቀናውን በማሰብ ፣ በአደራዳሪነት ውይም በታዛቢነት ለማገልገል ፍላጎት ያላቸው ይኖሩ ይሆናል። ግን የዚህን ጉድ በዚህ ደራጃ መሆኑ ሲገባቸው ፣ ቀኝ ወደ-ኋላ ማለታቸው አይቀሬ ነው። ይሄም ሌላኛው ትዝብት ነው። – ይዚህ ጽሁፍ አንባቢያን ፣ ከላይ የገለፅኩት በአብዛኛው ፣ በዚህ ድርድር ላይ ፍላጎት ላላቸው ገና ከጅምሩ ፣ይሄን ሃሳቤን ለማጋራት በቻልኩት አቅም ሁሉ ሞክሪያለው። ይታይ የነበረ ስእተት ወቅቱን ጠብቆ በገባኝ መጠን እርማት እንዲደረግበት ጥረት አድርጊያለው ። ከዛሬ ነገ የሚሻል ነገር ካለ ብዬ ለመታገሥ ለራሴ እድል ሰጥቻለው። ይሁን እንጂ በእኛ ሰፈር የአራዳ ቋንቋ ( ወፍ የለም)። ስለዚህም ዓላማውን ለሳተ ድርድር ከዚህ በላይ መንፈራገጥ ትርፉ ትዝብት ነው !!! በማላት የዚህ ጽሁፍ ማብቂያ ይሄ ይሁን፣ ለሌላው ደግሞ በሌላ ቀን ። አንባቢያን ከአክብሮት ጋር የምጠይቀው ይህ የግል ሃሳቤ እንጂ የይትኛው ፓርቲ አቋም የሚመለከት አይደለም።(ይድነቃቸው ከበደ) – ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !!!

ወያኔ የዩንቨርሲቲ መምህራንና ሠራተኞችን ጥልቅ ተሃድሶ በሚል ስብሰባ ጠምዶ ይዟል፤ muluken tesfaw

ወያኔ የዩንቨርሲቲ መምህራንና ሠራተኞችን ጥልቅ ተሃድሶ በሚል ስብሰባ ጠምዶ ይዟል፤
muluken tesfaw . የትግሬ ወያኔ መንግሥት በሁሉም ዩንቨርሲቲዎች ያሉ መምህራንና ሠራተኞችን ጥልቅ ተሃድሶ በሚል ስብሰባ ጠምዶ እንደያዛቸው ከየዩንቨርሲቲዎቹ የሚወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ከወሎና ከዓለማያ ዩንቨርሲቲዎች የደረሱን መረጃዎች እንደሚያመለክቱት መንግሥት የሕዝብን ጥያቄ የመልካም አስተዳደርና የተገልጋዩ ሕብረተሰብ ውጣ ውረድ መማረር ነው በሚል ለሚዲያ ሽፋን ለመስጠት ደፋ ቀና እያለ ነው ብለዋል፡፡
ምሁራኑ እንደሚሉት ጥልቅ ተሃድሶ በሚል ለመገምገሚያ በቀረበው ሰነድ መሠረት በሕዝብ የተጠየቁ ጥያቄዎች ቦታ አልተሰጣቸውም ተብሏል፤ ‹‹ይልቁንም በመልካም አስተዳደር እጦት በሚል እየጠሸፈኑ ነው›› ሲሉ ተችተዋል፡፡
በወሎ ዩንቨርሲቲ በሁለቱም ግቢዎች ያሉ መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች በስብሰባው ‹‹ከሕዝብ ጋር የመታረቅ ፍላጎት የሌለው መንግሥት›› ሲሉ ተችተዋል፡፡ በዓለማያ ዩንቨርሲቲ አፍረንቀሎ አዳራሽ መምህራን፣ በኦዲተሪየም ወይም አሮጌው አዳራሽ የአስተዳደር ሠራተኞች እንዲሁም በሴቶች ላይብራሪ ደግሞ የጽዳትና የጥበቃ ሠራተኞች ከትላንት ጀምሮ ስብሰባ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የዐማራ ተወላጅ መምህራን በዘራቸው ምክንያት እየደረሰባቸው ያለውን በደል አንስተዋል ተብሏል፡፡
ምሁራኑ በውጭ በነጻነት የሚኖሩ ምሁራን አስተያየታቸውን ይሰጡበት ዘንድ የተሃድሶ ሰነድ የተባለውን ዶክመት አብረው የላኩ ሲሆን ከፊሉ ከዚህ ዜና ጋር አብሮ ተያይዟል፡፡

Tuesday, March 7, 2017

የኢሕአዴግ ስራ አስፈፃሚ ትናንት የጀመረውን ስብሰባ ዛሬም ቀጥሏል | የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በተመለከተ ውሳኔ ሊተላለፍ ይችላል

(ቢቢኤን) የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በትናንትናው ዕለት መደበኛ ስብሰባውን መጀመሩ ተገለጸ፡፡ የአራት ፓርቲዎች ውህድ የሆነው ፓርቲው በሚኖረው የሶስት ቀናት ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ታውቋል፡፡ ፓርቲው ውሳኔ ያሳልፍባቸዋል ተብሎ ከተያዙ ጉዳዮች መካከል አንዱ አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንደሚሆን ምንጮች ገልጸዋል፡፡
በመጪው መጋቢት 28 ቀን 2009 ስድስተኛ ወሩን የሚይዘው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ፣ ይነሳ ወይስ ይቀጥል በሚለው ጉዳይ ላይ መንግስት ወጥ አቋም ሳይዝ ቆይቷል፡፡ ለዚህም እንደ ምክንያት የሚጠቀሰው የኢህአዴግ ባለስልጣናት በአስቸኳይ አዋጁ ዙሪያ የተለያየ አቋም መያዛቸው እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡ አብዛኞቹ የህወሓት ባለስልጣናት አዋጁ ከስድስት ወርም በላይ እንዲቆይ ፍላጎት ያላቸው ሲሆን፣ ከፊሎቹ ደግሞ የውጭ ለጋሾችን ተፅዕኖ በመፍራት አዋጁ ከስድስት ወር በላይ ባይቀጥል ፍላጎት እንዳላቸው ምንጮች ይገልጻሉ፡፡
አዋጁ እንደ አጠቃላይ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ሲታይ ደግሞ፣ አዋጁ ይፋ ሲደረግ የተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ከተጠናቀቀ በኋላ፣ ባይቀጥል የሚል በላጭ አመለካከት እንዳለም መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በኋላ ሀገሪቱ ‹‹መረጋጋቷን›› ሲገልጹ የሚደመጡት የኢህአዴግ ባለስልጣናት፣ ሀገሪቱ መረጋጋቷን ለውጭ ዲፕሎማቶች እና ለጋሽ ሀገራት ለማሳየት አዋጁን የማንሳት ፍላጎታቸው አመዝኗል ተብሏል፡፡ ሆኖም በፓርቲው ውስጥ ያለው ወጥ ያልሆነ አቋም፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በተመለከተ በቀጣይ የስብሰባ ቀናት ምን ዓይነት ውሳኔ ሊተላለፍ እንደሚችል ከወዲሁ ለመገመት አዳጋች ሆኗል፡፡ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ይፋ ከተደረገ በኋላ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች መገደላቸው፣ በሺዎች የሚቆጠሩ መታሰራቸው እና በርካቶችም ሀገር ጥለው መሰደዳቸው ይታወቃል፡፡

Wednesday, March 1, 2017

በባሕር ዳር ዩንቨርሲቲ ፖሊ ግቢ የማስጠንቀቂያ ወረቀት ተብትኖ አድሯልMuluken Tesfaw



በባሕር ዳር ዩንቨርሲቲ ፖሊ ግቢ የማስጠንቀቂያ ወረቀት ተብትኖ አድሯል፤ Muluken Tesfaw
ዛሬ የካቲት 22 ቀን 2009 ዓም ማለዳውን መረጃ የላኩልን ሰዎች እንዳመለከቱት የወያኔ ግፍ ደግፈው ለሚንቀሳቀሱ የትግራይ ተማሪዎች ማስጠንቀቂያ አዘል መልእክት ተበትኖ ማደሩን ሰምተናል። በዩንቨርሲቲው ግቢ ሲበተን ያደረው ወረቀት የጽሑፍ ይዘት የሚከተለው ነው፤
ማስጠንቀቂያ ለትግራይ ተማሪዎች
በትግራይ የአገዛዝ ስር የወደቀችው አማራ በህዝቡ ላይ ህወሀት ከፍተኛ የዘር ማጥፋት ወንጀል እየፈፀመበት መሆኑን ደጋግመን መናገራችን ይታወቃል፡፡ነገር ግን መናገራችን እንደ በደል ተቆጥሮብን በደሉ እየገፋ መምጣቱን ሆን ብሎ አሰቀጥሎታል፡፡ እኛም እናንተ የትግራይ ተማሪዎች አትዮጵያዊ ስሜት ይኖራችኋል ብለን በዝምታ ስንከታተላችሁ ብንቆይም እናንተ ግን የእኛ ሞት ለእናንተ ደስታ ሆኖላችሁ በ 19/06/09 ዓ.ም በባህር-ዳር ከተማ የሙዚቃ ድግስ አዘጋጅታችሁ ስትዘፍኑ መዋላችሁ የአማራ መሞት ለእናንተ ደስታ መሆኑን አረጋግጠናል፡፡ ከዚህ በኋላ በጎንደር እየተገደሉ ያሉ ገበሬዎች ሞት፤ በባህርዳር ቤት ለቤት እየተዞረ ሰው ለቀማ ካላቆመ፤ በአማራ ክልል የምትገኙ የትግራይ ተወላጆች በሙሉ ቅጣቱን እናንተ ላይ እንደምንጥለው እንድታውቁ፤ አንድም የትግራይ ተወላጅ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ከግቢ ወጥቶ ሲዝናና ፣ ቤተ-ክርስቲያን ሲሄድ፤ በትግሬ ስም ስብሰባ የምትሰበሰቡ ከሆነ እየተከታተልን እርምጃ የምንወስድ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
አማራ ወደፊት!!!!!