Tuesday, March 7, 2017

የኢሕአዴግ ስራ አስፈፃሚ ትናንት የጀመረውን ስብሰባ ዛሬም ቀጥሏል | የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በተመለከተ ውሳኔ ሊተላለፍ ይችላል

(ቢቢኤን) የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በትናንትናው ዕለት መደበኛ ስብሰባውን መጀመሩ ተገለጸ፡፡ የአራት ፓርቲዎች ውህድ የሆነው ፓርቲው በሚኖረው የሶስት ቀናት ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ታውቋል፡፡ ፓርቲው ውሳኔ ያሳልፍባቸዋል ተብሎ ከተያዙ ጉዳዮች መካከል አንዱ አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንደሚሆን ምንጮች ገልጸዋል፡፡
በመጪው መጋቢት 28 ቀን 2009 ስድስተኛ ወሩን የሚይዘው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ፣ ይነሳ ወይስ ይቀጥል በሚለው ጉዳይ ላይ መንግስት ወጥ አቋም ሳይዝ ቆይቷል፡፡ ለዚህም እንደ ምክንያት የሚጠቀሰው የኢህአዴግ ባለስልጣናት በአስቸኳይ አዋጁ ዙሪያ የተለያየ አቋም መያዛቸው እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡ አብዛኞቹ የህወሓት ባለስልጣናት አዋጁ ከስድስት ወርም በላይ እንዲቆይ ፍላጎት ያላቸው ሲሆን፣ ከፊሎቹ ደግሞ የውጭ ለጋሾችን ተፅዕኖ በመፍራት አዋጁ ከስድስት ወር በላይ ባይቀጥል ፍላጎት እንዳላቸው ምንጮች ይገልጻሉ፡፡
አዋጁ እንደ አጠቃላይ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ሲታይ ደግሞ፣ አዋጁ ይፋ ሲደረግ የተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ከተጠናቀቀ በኋላ፣ ባይቀጥል የሚል በላጭ አመለካከት እንዳለም መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በኋላ ሀገሪቱ ‹‹መረጋጋቷን›› ሲገልጹ የሚደመጡት የኢህአዴግ ባለስልጣናት፣ ሀገሪቱ መረጋጋቷን ለውጭ ዲፕሎማቶች እና ለጋሽ ሀገራት ለማሳየት አዋጁን የማንሳት ፍላጎታቸው አመዝኗል ተብሏል፡፡ ሆኖም በፓርቲው ውስጥ ያለው ወጥ ያልሆነ አቋም፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በተመለከተ በቀጣይ የስብሰባ ቀናት ምን ዓይነት ውሳኔ ሊተላለፍ እንደሚችል ከወዲሁ ለመገመት አዳጋች ሆኗል፡፡ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ይፋ ከተደረገ በኋላ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች መገደላቸው፣ በሺዎች የሚቆጠሩ መታሰራቸው እና በርካቶችም ሀገር ጥለው መሰደዳቸው ይታወቃል፡፡

Wednesday, March 1, 2017

በባሕር ዳር ዩንቨርሲቲ ፖሊ ግቢ የማስጠንቀቂያ ወረቀት ተብትኖ አድሯልMuluken Tesfaw



በባሕር ዳር ዩንቨርሲቲ ፖሊ ግቢ የማስጠንቀቂያ ወረቀት ተብትኖ አድሯል፤ Muluken Tesfaw
ዛሬ የካቲት 22 ቀን 2009 ዓም ማለዳውን መረጃ የላኩልን ሰዎች እንዳመለከቱት የወያኔ ግፍ ደግፈው ለሚንቀሳቀሱ የትግራይ ተማሪዎች ማስጠንቀቂያ አዘል መልእክት ተበትኖ ማደሩን ሰምተናል። በዩንቨርሲቲው ግቢ ሲበተን ያደረው ወረቀት የጽሑፍ ይዘት የሚከተለው ነው፤
ማስጠንቀቂያ ለትግራይ ተማሪዎች
በትግራይ የአገዛዝ ስር የወደቀችው አማራ በህዝቡ ላይ ህወሀት ከፍተኛ የዘር ማጥፋት ወንጀል እየፈፀመበት መሆኑን ደጋግመን መናገራችን ይታወቃል፡፡ነገር ግን መናገራችን እንደ በደል ተቆጥሮብን በደሉ እየገፋ መምጣቱን ሆን ብሎ አሰቀጥሎታል፡፡ እኛም እናንተ የትግራይ ተማሪዎች አትዮጵያዊ ስሜት ይኖራችኋል ብለን በዝምታ ስንከታተላችሁ ብንቆይም እናንተ ግን የእኛ ሞት ለእናንተ ደስታ ሆኖላችሁ በ 19/06/09 ዓ.ም በባህር-ዳር ከተማ የሙዚቃ ድግስ አዘጋጅታችሁ ስትዘፍኑ መዋላችሁ የአማራ መሞት ለእናንተ ደስታ መሆኑን አረጋግጠናል፡፡ ከዚህ በኋላ በጎንደር እየተገደሉ ያሉ ገበሬዎች ሞት፤ በባህርዳር ቤት ለቤት እየተዞረ ሰው ለቀማ ካላቆመ፤ በአማራ ክልል የምትገኙ የትግራይ ተወላጆች በሙሉ ቅጣቱን እናንተ ላይ እንደምንጥለው እንድታውቁ፤ አንድም የትግራይ ተወላጅ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ከግቢ ወጥቶ ሲዝናና ፣ ቤተ-ክርስቲያን ሲሄድ፤ በትግሬ ስም ስብሰባ የምትሰበሰቡ ከሆነ እየተከታተልን እርምጃ የምንወስድ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
አማራ ወደፊት!!!!!

Sunday, February 26, 2017

ማጭበርበር የማይሰለቸው ወያኔ የውጪ ሀገር ስደተኞችን ለማቋቋም እየሰራሁ ነው አለ source mereja.com



ማጭበርበር የማይሰለቸው ወያኔ የውጪ ሀገር ስደተኞችን ለማቋቋም እየሰራሁ ነው አለ. የራሱን ዜጎች እያባረረ የሌላ አገር ስደተኞችን የሚያቋቁም ደነዝ አገዛዝ እድሜው አጭር ነው።
– የአውሮፓ ህብረትና ኔዘርላንድ ለስደተኞች ማቋቋሚያ የ720 ሚ. ብር ድጋፍ አድርገዋል
– ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ስደተኞች በየጊዜው እየጨመሩ ነው
ማጭበርበር የማይሰለቸው ወያኔ የውጪ ሀገር ስደተኞችን ለማቋቋም እየሰራሁ ነው አለ   የራሱን ዜጎች እያባረረ የሌላ አገር ስደተኞችን የሚያቋቁም ደነዝ አገዛዝ እድሜው አጭር ነው።  የአውሮፓ ህብረትና የኔዘርላንድ ኤምባሲ፤ በኢትዮጵያ የሚገኙ የውጭ ሀገር ስደተኞችን ለማቋቋምና ስደተኞቹን እያስተናገዱ ያሉ አካባቢዎችን ለመደገፍ የሚውል የ720 ሚሊዮን ብር ፕሮጀክት ይፋ ያደረገ ሲሆን መንግስት በበኩሉ፤ ስደተኞችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ አሰራሮችን እያዘጋጀ መሆኑን አስታውቋል፡፡
በአውሮፓ ህብረትና በኔዘርላንድ ኢምባሲ ይደገፋል የተባለውን የክልላዊ ልማትና እንክብካቤ ፕሮጀክትን በአዲስ አበባ ይፋ ያደረጉት በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት ልኡክ መሪ አምባሳደር ቻንታል ኧብረት፤ ኢትዮጵያ ለምትከተለው “ስደተኞችን እጅን ዘርግቶ የመቀበል” ፖሊሲ አድናቆት እንዳላቸው ገልፀው፤ ህብረቱም ይህን መነሻ አድርጎ ድጋፉን መለገሱን ተናግረዋል፡፡ ማጭበርበር የማይሰለቸው ወያኔ የውጪ ሀገር ስደተኞችን ለማቋቋም እየሰራሁ ነው አለ
720 ሚሊዮን ብሩ ስደተኞቹን ለመንከባከቢያና ስደተኞቹን ተቀብለው እያስተናገዱ ያሉ ማህበረሰቦችን ለመደገፍ እንደሚውል የተገለፀ ሲሆን ለትምህርት፣ ለውሃና ለኃይል አቅርቦት እንዲሁም ለሌሎች የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎች ይውላል ተብሏል፡፡  የዚህ ፕሮጀክት ተጠቃሚዎች ስደተኛ ተቀባይ የሆኑት የትግራይ፣ አፋርና የሱማሌ ክልል ሲሆኑ የኤርትራና የሶማሊያ ስደተኞች የዚህ ፕሮግራም ዋነኛ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል፡፡
በስነ ስርአቱ ላይ ተገኝተው ስደተኞችን በተመለከተ መንግስት እያከናወናቸው ያሉ መርሃ ግብሮችን ይፋ ያደረጉት የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ጽ/ቤት ም/ዳይሬክተር አቶ ዘይኑ ጀማል፤ በአሁን ወቅት የደቡብ ሱዳን፣ የኤርትራ፣ የሱማሊያ፣ የኬንያና የሌሎች ሀገራትን ጨምሮ 8 መቶ ሺህ ስደተኞች በኢትዮጵያ በተለያዩ ካምፖች እንደሚገኙ ጠቁመው መንግስት ስደተኞችን ማቋቋም የሚያስችል ፕሮግራም መንደፉን አስረድተዋል፡፡ እ.ኤ.አ በመስከረም 2016 ስደተኞችን አስመልክቶ በተደረገው የዓለም መሪዎች ስብሰባ ላይ፤ ኢትዮጵያ ስደተኞችን ለማቋቋም ቃል በገባችው መሰረት፡ የተለያዩ መርሃ ግብሮችን መቅረጿን ያመለከቱት አቶ ዘይኑ፤ ከስደተኞቹ 10 በመቶ ያህሉ (80 ሺህ)  ከካምፕ ውጪ የመኖር መብት ተጠቃሚ እንዲሆኑ፣ የስራ ፍቃድና፣ የነዋሪነት መታወቂያ ደብተር እንዲያገኙ መታቀዱን አስረድተዋል፡፡
አድልኦ ሳይደረግ የሁሉም ሀገር ስደተኞች ከመጀመሪያ ደረጃ አንስቶ እስከ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ድረስ ዘልቀው የትምህርት እድል እንዲያገኙ እንዲሁም በመስኖ ሊለማ የሚችልና 100 ሺህ ስደተኞችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሬት የሰብል ልማት እንዲያለሙበት ማዘጋጀቱን አስታውቀዋል፡፡
በሀገሪቱ ከሚገነቡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች መካከል የተወሰኑት ከሚቀጥሯቸው ሰራተኞች 30 በመቶዎቹ ስደተኞች እንዲሆኑ እንደሚደረግም ተገልጿል፡፡ ለመቶ ሺህ ሰዎች ከሚፈጠረው የስራ እድል ውስጥ 30 ሺህ ያህሉን ስደተኞች እንዲጠቀሙበት ለማድረግ ኢትዮጵያ ቃል ገብታለች ተብሏል፡፡ ለዚህ አይነቱ የሥራ ዕድል ከአውሮፓ ህብረት 50 ሚሊዮን ዩሮ እርዳታ  ከአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ 200 ሚሊዮን ዶላር ብድር እንደሚገኝም አምባሳደር ሻንታል በንግግራቸው ጠቁመዋል፡፡
መንግስት ስደተኞች የደህንነት ስጋትም ሆነ የዜጎች ተፎካካሪ ናቸው የሚል እምነት እንደሌለው ገልፀው፤ ስደተኞቹን አደራጅቶ የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዷል ብለዋል፡፡
በደቡብ ሱዳንና በሶማሊያ ካለው ድርቅ ጋር በተገናኘም በቀጣይ ጊዜያት በርካታ ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የጠቆሙት አቶ ዘይኑ፤ የዝግጁነት እቅድ አውጥተን እየሰራን ነው ብለዋል፡፡ ከደቡብ ሱዳን ብቻ ባለፉት 5 ወራት፣ ከ58 ሺህ በላይ ተጨማሪ ስደተኞችን ተቀብለናል ብለዋል አቶ ዘይኑ፡፡
በጋምቤላ ለእርሻ ኢንቨስትመንት ለባለሀብቶች በተሰጠ መሬት ላይ ስደተኞች እየሰፈሩ ነው የሚለው አቤቱታ ሀሰተኛ መሆኑንም ም/ዳይሬክተሩ ገልፀው፤ ስደተኞቹ ከእንዲህ ያሉ መሬቶች ጋር ግንኙነት የላቸውም ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ ስደተኞችን ተቀብላ በማስተናገድ ከአፍሪካ 2ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠች ሲሆን ከ3 መቶ ሺህ በላይ የደቡብ ሱዳን፣ 250 ሺህ የሶማሊያና 265 ሺህ የኤርትራ ዜጎችን ጨምሮ የኬንያ፣ ሱዳንና የአረብ ሀገራት ስደተኞች ይገኛሉ፡፡  ማጭበርበር የማይሰለቸው ወያኔ የውጪ ሀገር ስደተኞችን ለማቋቋም እየሰራሁ ነው አለ የራሱን ዜጎች እያባረረ የሌላ አገር ስደተኞችን የሚያቋቁም ደነዝ አገዛዝ እድሜው አጭር ነው

Thursday, February 23, 2017

ህወሃት በዱባይ አገር በሚገኘው እጅግ ዘመናዊ አለማቀፍ ሆቴል ውስጥ የምስረታ በአሉን ሊያከብር ነው source abbay media

ፎቶ ከፋይል
በህወሃት ኩባንያ ሙሉ ድጋፍ እና በኢትዮጵያ አየር መንገድ ትብብር ህወሃት የተመሰረተበትን 42ኛ አመት የልደት በአል በአለማችን እጅግ ዘመናዊና ውድ በሚባለው ቡርጂ አል አራብ ጁሚራህ ሆቴል ውስጥ ከአርብ እስከ እሁድ እንደሚያከብር ምንጮች ገልጸዋል።
በልዩ ትእዛዝ በተዘጋጁ አምስት አውሮፕላኖች የህወሃት መስራች አባላትና ባለስልጣኖች እንዲሁም ወጣት የህወሃት ደህንነቶች ባለሃብቶችና ጠንካራ አባላት ከዛሬ ረቡዕ ጀምሮ ወደ ዱባይ በረራ ያደርጋሉ።
እንግዶቹ ዘመናዊ በሚባሉት Abidos Hotel ፣ Apartment Dubailand፣ Saffron Boutique Hotel እና Fortune Karama Hotel መኝታ የተያዘላቸው ሲሆን በቆይታቸው ሙሉ ወጪያቸው በድርጅታቸው ኩባንያ ይሸፈንላቸዋል።
ህወሃት ህዝብ በተራበበትና ከፍተኛ ችግር ላይ በወደቀበት በዚህ ወቅት በአሉን በውጭ አገር ለማክበር የመረጠው ከህዝብ አይን ለመሸሽና ከትችት ለመዳን ሲባል መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል።
በርካታ የህወሃት ባለስልጣናት ድርጅታቸው በአሉን በውጭ ለማክበር ማሰቡን በአድናቆት ተመልክተውታል።“ በያመቱ በአገር ውስጥ ከሚደረገው አሰልቺ በአል የተለየ ዝግጅት ማዘጋጀቱ፣ ለነጻነቱም ለምቾቱም ጥሩ ነው” ሲል አንድ ተጋባዥ እንግዳ አድናቆቱን ገልጿል።
በአለማችን የናጠጡ ሃብታሞችና ታዋቂ ሰዎች በሚስተናገዱበት ሆቴል ህወሃት ለሙዚቃ ዝግጅቱ በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ያወጣል።
በሌላ በኩል በደቡብ፣ ኦሮምያና ሶማሊያ ክልሎች የረሃቡ ሁኔታ እጅግ አስከፊ ሆኖ መቀጠሉን የሚደርሱን መረጃዎች ያመለክታሉ።

Wednesday, February 8, 2017

በሰሜን ጎንደር በምዕራብ በለሳ የሚኖሩ ዐማሮች በወያኔ መከላከያ ሠራዊት ቤታቸውና ንብረታቸው እየወደመ ይገኛል፤ Muluken Tesfaw –#AmharaResistance

   Image result for gonder demonstration



Muluken Tesfaw#AmharaResistance በሴረኞች የዐማራ ሕዝብ ተጋድሎ አይቀለበስም!
ከጥር 29 ቀን 2009 ዓ/ም በሰሜን ጎንደር በምዕራብ በለሳ የሚኖሩ ዐማሮች በወያኔ መከላከያ ሠራዊት ቤታቸውና ንብረታቸው እየወደመ ይገኛል፤ የሚያሳዝነው ደግሞ ሌላው ወገናቸው ችግራቸው በሚገባ ያልታወቀ መሆኑ ነው፡፡
ከዚህ የከፋም ችግር አለ፤ የዐማራ ተጋድሎ አስተባባሪ የጎበዝ አለቆች በድብቅ ስብሰባ መጥራታቸውን ወያኔን እንቃወማለን በሚሉ ነገር ግን ደግሞ የዐማራ ሕዝብን ዐማራዊ ተጋድሎ ለቡድናቸው ወይም ለድርጅታቸው ሕልውና አሉታዊ ተጽዕኖ ያሳድራሉ በሚባሉ ወገኖች ጠቋሚነት መሆኑ ነው፡፡
ከዐማራ ተጋድሎ አስተባባሪ የጎበዝ አለቆች ጋር በመተባበር አንድ ስብሰባ እንዲጠራ ይደረጋል፤ ብዙዎቹ የጎበዝ አለቆች ተጠራጥረው ሳይሔዱ ቀሩ፡፡ ሆኖም ሁሉም ይመጣሉ በተባለበት ሰዐት የወያኔ ወታደሮች እስከአፍንጫቸው ታጥቀው በለሳ መሸጉ፡፡ ሁሉንም ለማስቀረት ቢሞከርም በዐማራ ታጋዮች ላይ ምንም ዓይነት የሰው ሕይወት ሳይጠፋ በጀግንነትና በወኔ የወያኔን አጥር ሰብረው ሊወጡ ችለዋል፡፡ ሆኖም ከመካከል የነበረ አንድ ሰው ጠፍቷል ተብሏል፡፡
የሚያሳዝነው ግን ከቅዳሜ ዕለት ጀምሮ የበለሳ ገበሬዎች ቤትና ንብረት በግፍ እየወደመ ነው፡፡ እስካሁን ባለን መረጃ መሠረት ከሃያ የማያንሱ ቤቶች በኮዛ አቦ አካባቢ በከባድ መሣሪያ ወድሟል፡፡ ከመቶ ያላነሱ ቤተሰቦችም ያለ መጠለያ ተበትነዋል፡፡ ምን ዓይነት ችግር ውስጥ እንዳሉና እንደሰነበቱ ሌላው ዐማራም አላወቀውም ገና፡፡
የዐማራ ተጋድሎን ለማኮላሸት ለወያኔ መረጃ በመስጠት የተባበሩ አካላት በዐማራነት መደራጀትን እየኮነኑ እንደገና እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ ስንሰማ ደግሞ የበለጠ አዝነናል፡፡ ይህ ጉዳይ በሚገባ እየተጣራ በመሆኑ የዐማራ ተጋድሎ አስተባባሪ የጎበዝ አለቆች ትምህርት የሚወስዱበት አጋጣሚ ይሆናል፡፡
እንደማጠቃለያ ማንም ሰው (ቡድን) የፈለገውን ርዕዮተ ዓለምና አደረጃጀት ይዞ መጓዝ ይችላል፤ ሆኖም በዐማራ ሕዝብ ላይ የሚሸርቡትን ሴራ ማቆም አስፈለጊም ብቻ ሳይሆን ግዴታም ጭምር ነው፡፡ የዐማራ ሕዝብ ትግል ላይቀለበስ ተቀጣጥሏል፡፡
የዐማራ ሕዝብ ትግል ያሸንፋል//

Tuesday, February 7, 2017

የበዓሉ ግርማ ቮልስ ዋገን 7845 ቆንጅት ስጦታው



Image may contain: car and outdoor
የበዓሉ ግርማ ቮልስ ዋገን 7845
ማርታ መኮንን – ይህች የምትመለከቷት ነጭ ፤ መቀመጫዋ ቀይ ቮልስ ዋገን የበዓሉ ግርማ ነበረች። የበፊት ታርጋዋ 7845 ነበር ፤ አሁን ከፊቱ አንድ ተጨምሮ 17845 ነው። በዓሉ ካረፈ በኋላ ነው ባለቤቱ ወ/ሮ አልማዝ በሦስት ሺ ብር ለአንድ የቀድሞ ኮሎኔል የሸጡላቸው። ኮሎኔሉ ‹‹ብር ሳልከፍል ነው ከጊቢ ይዤ የወጣሁት። በነጋታው ነው ገንዘቡን የከፈልኩት›› ይላሉ።
ኮሎኔሉ ሌሎች መኪኖች አሏቸው። ቢሆንም ለዚህች ታሪካዊ ቮልስ ልዩ ፍቅር እና ክብር አላቸው። በእረፍታቸው ከወዳጆቻቸው ጋር ዘና ማለት ሲፈልጉ ቮልሷን ይዘው ነው የሚወጡት። ሴፌሪያን ነው የሚወስዷት ከተበላሸች። የበዓሉ ፋውንዴሽን ሰዎች ከአሜሪካ መጥተው አንድ ሚልየን ብር ሽጡልን ብለዋቸው አይሆንም ብለው መልሰዋል።

Monday, February 6, 2017

ኢትዮጵያ ለአደጋ ተጋልጣለች – 948 ሚ. ዶላር እርዳታ ያስፈልጋል – 300 ሺ ህፃናት ልዩ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል ቆንጅት ስጦታው



ኢትዮጵያ ለአደጋ ተጋልጣለች – 948 ሚ. ዶላር እርዳታ ያስፈልጋል – 300 ሺ ህፃናት ልዩ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል

– ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የእርዳታ ጥሪ ቀርቧል
– ድርቁን ለመቋቋም 948 ሚ. ዶላር እርዳታ ያስፈልጋል
– 300 ሺ ህፃናት ልዩ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል
– የግል ባለሃብቶች እርዳታ ይፈለጋል
ኢትዮጵያ አሁንም በአየር ፀባይ ለውጥ ሳቢያ ከተከሰተው የድርቅ አደጋ መላቀቅ አለመቻሏን ያስታወቀው የተባበሩት መንግስታት የምግብና እርሻ ድርጅቱ፤ አለማቀፉ ማህበረሰብ ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ የእርዳታ እጁን እንዲዘረጋ አሳስቧል፡፡ መንግስት በበኩሉ፤ ድርቁን ለመቋቋም ከ948 ሚሊዮን ዶላር በላይ ያስፈልጋል ብሏል፡፡
በአሁን ወቅት በድርቁ የተጎዳው 5.6 ሚሊዮን ህዝብ ሲሆን የበልግ አዝመራ ጥሩ ካልሆነ የተጎጂው ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ተሰግቷል፡፡ ድርቁ በኢትዮጵያ ሶማሌ፣ በኦሮሚያ  በደቡብ ክልል ቆላማ አካባቢዎች የተከሰተ መሆኑን ለአዲስ አድማስ ያብራሩት የፌደራል አደጋ መከላከልና ዝግጁነት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሳ፤ በአሁኑ ወቅት መንግስት አስፈላጊውን እርዳታ እያደረገ ነው ብለዋል።
ቀደም ብሎ በተወሰኑ አካባቢዎች በድርቁ ሳቢያ ከብቶች መሞታቸውን የጠቆሙት አቶ ምትኩ፤ ለከብቶች መኖ በማቅረብ ብቻ አደጋውን መቋቋም የሚቻል ባለመሆኑ፣ ከብቶች ሳይጎዱ ለገበያ ለማቅረብ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በአጠቃላይ ድርቁን ለመቋቋም ከሚያስፈልገው 948 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ የክልልና የፌደራል መንግስታት 75 ሚሊዮን ዶላር መመደባቸውን የገለፁት ኮሚሽነሩ፤ ለተጎጂዎች በተለያየ ይዘት የእለት እርዳታ ራሽን ክፍፍል እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በዚህ የድርቅ አደጋ የግል ባለሀብቶች እርዳታ እንደሚፈለግ አቶ ምትኩ ጠቁመዋል፡፡
ለእያንዳንዱ ግለሰብ 15 ኪ. ግራም ስንዴ፣ ለነፍሰ ጡር ሴቶችና ህፃናት 1.5 ኪ.ግ አልሚ ምግብ በነፍስ ወከፍ እየተከፋፈለ መሆኑን ለአዲስ አድማስ የጠቆሙት አቶ ምትኩ፤ በድርቁ 3 መቶ ሺ ህፃናት እርዳታ እንደሚፈልጉ፤ አስታውቀዋል፡፡
በእርዳታ አቅርቦት ላይ መንግስት የመሪነቱን ድርሻ የሚይዝ ቢሆንም የውጭ እርዳታም እንደሚጠበቅ የጠቆሙት ኮሚሽነሩ፤ የተረጅዎች ቁጥር መጨመርና መቀነስን የሚወስነው ቀጣዩ የበልግ አዝመራ ነው ብለዋል፡፡ በደጋና ወይናደጋ የሃገሪቱ ክፍሎች በቂ የግብርና ምርት በመኖሩ አብዛኛው የእርዳታ እህል ግዢ፣ ከሃገር ውስጥ እንደሚሆንም ተገልጿል፡፡
አዲሱ የተባበሩት መንግስታት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ ሰሞኑን በአዲስ አበበ ተገኝተው በሰጡት መግለጫ፤ በኢትዮጵያ የተከሰተው ድርቅ አሳሳቢ መሆኑን በመጥቀስ፣ አለማቀፉ ህብረተሰብ የእርዳታ ርብርብ እንዲያደርግ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡