Thursday, October 6, 2016

ኢትዮጵያዊያን በቢሾፍቱ ለተጨፈጨፉ ወገኖች የሻማ ማብራት ዝግጅት አደረጉ




img_5255img_5255
ቁጥራቸው በሽዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን በትናንትናው ምሽት ዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ውስጥ በመሰባሰብ ዋይት ሃውስ ቤተመንግስት ፊት ለፊት ተገኝተው የእሬቻን በዓል ቢሾፍቱ ከተማ ውስጥ በማክበር ላይ በነበሩ የኦሮሞ ብሔረሰብ አባላትና ሌሎችም ታዳሚዎች ላይ በአጋዚ ጦር ጥይት የረገፉትን ወገኖች በማሰብ የጸሎትና የሻማ ማብራት ዝግጅት አድርገዋል። በዝግጅቱ ላይ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን፣ ከኢትዮጵያ ሙስሊም ሐይማኖት፣ ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን የተወከሉ አባቶች ልብ የሚነካ፣ የሚያበረታታና የሚያጽናና መልዕክቶችን አስተላልፈዋል።
በዚህ ዝግጅት ላይ የኢትዮጵያዊያን አንድነት ጎልቶና ደምቆ የታየበት ከመሆኑም በላይ የህዝቡ ጠላት ወያኔ ብቻ መሆኑ ከተለያዩ የማህበረሰብ ተወካዮች በተላለፈው መልክት ተገልጿል። በተለይም የኦሮሞና የአማራ ህዝብ ድርና ማግ መሆናቸውና እንደማይነጣጠሉ እንዲሁም አንዱ ከሌለ ሌላው እንደማይኖር የተረጋገጠበትና የታየበት መድረክ ነበር። (ስለዝግጅቱ የሚያሳዩ ተጨማሪ ፍቶግራፎች እንለቃለን

እሬቻ ለምን ቁጣ አስነሳ!









ከአማራ ክልል በሁለት መክና ሞልቶ እሬቻን ከኦሮሞ ወንድሞቻችን ጋር እናከብራለን ብሎ ይመጣሉ። ብሾፍቱ ወይም ደብሬዜይት እንደደረሱ የአባ ጌዳ ጽuፈት ቤት ይሄዱና አቶ በዬና ስንበቶን አናግሮ አላማቸዉንም ይነግሩአቸዋል። እሳቸዉም በደስታ ይቀበሉአቸዋል።
የወያኔ አንጀት አረረ፣ ቁጣቸዉንም በአቶ በዬና ሰንቤቶ ላይ አወረዱ። ኦሮሞና አማራ ደግሞ ከመቼ ወድህ ነዉ እሬቻን አብሮ የምያከብሩት አሉአቸዉ። እሳቸዉም ዛሬም ብንጀምር አልረፈደም አሉአቸዉ።
እነዝህ ሰዎች እሬቻ ላይ እንዳይገኙ፤ ከተገኙም ደግሞ ንግግር እንዳያደርጉ በማለት ወያነዎች ጥብቅ ትእዛዝ ሰጡ። አቶ በየናም ይህ የማህበረስብ ጉዳይ እንጅ መንግስትን የምመለከት አይደላም። ስለዝህ የህዝባችን ሀዘን የነሱ ሀዘን ስለሆኔ በደስታችንም ግዜ ከኛ ጋር ተደስቶ ብሄዱ ደስ ይለናል እንጅ ቅር አይለንም እያሉ ይከራከራሉ።

ይሄዳሉ፤ አይሄዱም ንግግር ያደርጋሉ አያደርጉም በምለዉ ጭቅጭቅ ረጅም ግዜ ሄዴ። ቀሮ ደግሞ በሳቸዉ መዘግዬት ምክንያት down down woyane, down down TPLF ማለት ጀመሬ። በስተመጨረሻም እንዳያችሁት፤ በግትርነቱ፤ በጭካነዉ በክፋቱ በአስለቃሽ ጭስ አይናችዉ አዉሮ ጥይት አርከፈከፉባቸዉ፤ ግማሹን ገደል ዉስጥ ጨመሩአቸዉ፤ ግማሹን ሀይቅ ዉስጥ ጣሉአችዉ።
ታድያ የሀዉዘን ጭፍጨፋ ና የብሾፍቱ ጭፍጨፋ ምን ይለየዋል



Image result for irreecha oromo

አዲስ አበባ ተቆላልፋለች – ፖሊስ እና ሰራዊቱ በሕዝብ ላይ አልተኩስም ብለዋል (ክንፉ አሰፋ)  



Addis Ababa protest
በሳምንቱ መግቢያ የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ብሄራዊ እርቅ እና ድርድር እንዲደረግ ጥሪ ማድረጉ ይታወሳል። አምስቱ የሕወሃት ቁንጮዎች ትእቢት የተሞላበት ምላሽ ነው የሰጡት። ከድርድር ይልቅ ከሕዝብ ጋር ጦርነት መግጠምን መርጠዋል። አብዛኛው የፖሊስ እና የሃገር መከላከያ ሰራዊቱ “ሕዝብ ላይ አልተኩስም” ማለታቸው የህወሃት አመራርን ጭንቅ ውስጥ አስገብተውታል።
አዲስ አበባ ተቆላልፋለች። በአራቱም አቅጣጫ በኩል የሚገባም የሚወጣም የለም። መንገዶች በሙሉ ተዘጋግተዋል። ስልክ እና ኢንተርኔት ጠፍቷል።
በአዲስ አበባ ዙርያ ባሉ ከተሞች ሰኞ መስከረም 23 ቀን የተጀመረውን ሕዝባዊ አመጽ ለማዳፈን በህወሃት የተወሰደው የአፈሳ እርምጃ አመጹን አላቆመውም። ሰኞ ማምሻውን በሺዎች የሚቆጠሩ ዘጎች ታፍሰው ወዳልታወቀ ስፍራ በወሰዳቸው ሳብያ አመጹ በዛሬው እለት ተባብሶ ቀጥሏል። የአካባቢ ፖሊሶችም ከሕዝብ ጋር በመሆን በአመመጹ እየተሳተፉ በመሆኑ የስራአቱን ቁንጮዎች ጭንቀት ውስጥ ከቷቸዋል።
ሰበታ ላይ የነበረው የቱርክ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ እና የሃይል ማመንጫ ኩባንያ በትናንትናው እለት መውደሙን ሮይተርስ ከስፍራው ዘግቧል። በሆለታ በነበረው አመጽ ሚስ ሻሮን ሬይ የተባለች አሜሪካው የግብርና ኤክፐርት መገደልዋንም ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቦ ነበር። ይህ ዜና በአለም የመገናኛ ብዙሃን ከተሰማ በኋላ ህወሃት የስልክ እና የኢንተርነት አገልሎት እንዲቋረጥ አድርጓል። የአመጹ ዜና ወደ ሌሎች እንዳይሰራጭ ታቅዶ የተደረገው ይህ ድርጊታቸው የህዝብን ቁጣ እያበረታው መጥቶ ካድሬዎችን እየለቀሙ መምታት እንዲጀመር አስተዋጽኦ አድርጓል።
ሕዝብ በጋራ ተነስቶ የህወሃት ተላላኪዎችን እያስጠነቀቀ ሲሆን እንቢ ያሉት ላይ እርምጃ እየተወሰደ ይገናል። የወንጂ ስኳር ፍብሪካ ከፉተኛ ቃጠሎ የደረሰበት ሲሆን፣ ኩሪፉቱ የሼክ አላዓሙዲን የከብት ማድለቢያ ንብረት ሙሉ በሙሉ ወድሟል። በቀርሳ ወረዳ አንድ የህወሃት ተላላኪ በህዝብ ተገድሏል፣ በሆሮ ጉድሩ እና በጉጂም የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች ላይ ሕዝብ እርምጃ ወስዶባቸዋል። በድሬ ዳዋ ዲፖ ጋዝ ስቴሽን ቤሳት ጋይቷል።
የናይጄሪያዊው ኪሎ ዲንጎቴ ንብረት የነበረው ዲንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካ ሙሉ በሙሉ በህዝባዊ አመጽ መውደሙን የአፍሪካ ሜድያ ኔትወርክ ዘግቧል። ጉጂ ዞን ያለው የሼክ አላሙዲን የወርቅ ማእድን በትላንትናው እለት መውደሙን ማህበራዊ ድረ-ገጾች ዘግበዋል።
ባዶ እጁን እየወጣ ሲገደል የነበረው የኦሮሞ ሕዝብ አሁን ራሱን ራሱን የሚከላከልበት መሳርያ እየያዘ መውጣቱን የሚደርሱን መረጃዎች ይጠቁማሉ። በአለም ገና ዳሽን ባንክ እና ከገዥው ፓርቲ ጋር ንክኪ ያላቸው መኪናዎች ተቃጥለዋል።
በአርሲ፣ በመቱ እና በጂማ በተማሪዎች የተቀሰቀሰው አመጽ እንደቀጠለ ነው። የጅማ ወህኒ ቤት ተቃጥሎ የፖለቲካ እስረኞች በሙሉ እንዲፈቱ የተደረገው ትላንት ምሽት ላይ ነበር።
አዲስ አበባ ከእሬቻው እልቂት በኋላ የሙት ከተማ መስላለች። የንግድ እንቀስቃሴ በሙሉ ቆሟል። ሱቆች ዝግ ናቸው፣ የህዝብ ትራንስፖርትም የለም። መርካቶም ጸጥ-ረጭ እንዳለች ነው። በዛሬው እለት ታክሲ በከተማዋ ባለመኖሩ አብዛኛው ሰው ስራ አልገባም። ከተወሰኑ የግል ትምህርት ቤቶች በስተቀር የመንግስት ትምህርት ቤቶች አሁንም ዝግ ሆነው እንዲቆዩ ተወስኗል። አንዳንድ የግል ት/ቤቶች ወላጆችንን ልጆቻቸውን ወደ ት/ቤት እንዳይልኩ እየመከሩ ይገኛሉ።
ለአዲስ ተማሪዎች ጥሪ ያደረገው የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ብቻ ነው። ሌላዎቹ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ተማሪ ገብቶ የመማሩ ጉዳይ የሚታሰብ አይደለም።
በደቡብ ወደ ሻሸመኔ እና ወደ አዋሳ የሚወስደው መንገድ እሁድ ጀምሮ ዝግ ነው። በሰሜን ሱልልታ፣ ለገዳዲ፣ ቦሌ ቡልቡላ፤ በም እራብ በአስኮ፣ በቡራዩ፣ ሰበታ፣ አለምገና፣ ብስራተ-ገብሬል፣ አየር ጤና፣ ወልሶ፣ ወደ ሆሳዕና እና ጅማ የሚወስዱ መንገዶች በሙሉ ተዘግተዋል። በዚያ የሚተላለፍ ተሽከርካሪ ቢገኝ የድንጋይ ናዳ ይወርድበታል።
አጋዚ ይህ ሕዝባዊ አመጽ ከቁጥጥር ውጪ ስለሆነበት አዲስ አበባን ብቻ ከብቦ እየጠበቀ፣ ንጹሃን ዜጋን በማፈስ ስራ ላይ ተጠምዷል።
ህወሃት በአማራው ሕዝብ ላይ በይፋ ያወጀው ጦርነት አልተሳካም። ራሱን ከመከላከል አልፎ አካባቢውን ከአጋዚ ነጻ እይደረገ ይገኛል። በርካታ የፖለቲካ እስረኞች ከእስር ነጻ ወጥተዋል። የባህርዳር ዩንቨርስቲ እስካሁን እንደተከበበ ነው። የኮሶበር ህዝብ የዳሽን ቢራን ጭኖ የነበረ ከባድ መኪና ከአገልግሎት ውጪ ሆኗል።
በባህር ዳር ወጣቶችን ሲያሰቃይ የነበረ የማንኩሳ ተወላጅ ማንነቱ ባልታወቀ አካል ተገድሎ መገኘቱ በማህበራዊ ድረ-ገጽ ተዘግቧል።
የህወሃት ባለስልጣናት አሸንዳን በርችት፣ እሬቻን በጥይት ካስተናገዱ በኋላ በወገን ላይ በደረሰው አሰቃቂ እልቂት መላው የአኢትይኦጵያ ህዝብ ብሄራዊ ሃዘን ላይ ነበር።
ብሄራው ሃዘን ላይ የነበረው ህዝብ ወደ ብሀራዊ አመጽ የገባ ይመስላል። ሰላማዊ ሕዝብን እንደ ግራዚያኒ፣ እንደ ሞሶሎኒ በጥይት እና በመርዝ ጭስ ከጨረሱ በኋላ በቴሌቭዥን ወጥተው አዝነናል እያሉ፣ ቁስልን የባሰ ሲነካኩበት ከዚህ ውጭ አማራጭ የለም። ሕወሃቶች ይልቁንም ለራሳቸው ይዘኑ። ሰላማዊውን ህዝብ እየጨረሱ ያሉት ሁሉ በተራቸው የሚያለቅሱበት ግዜ ሩቅ አይደለም። በደም የታጠበ እጃቸው ገና ሳታደርቅ በቴሌቭዥን ወጥተው በሟች አጽም ላይ መቀለዳቸው ሳያንስ በተለመደ የሽብርተኞች ዲስኩር ህዝብ ላይ እጅ መቀሰር ድፍረት ነው።
ግዜ ሊወስድ ይችል ይሆናል እንጂ እነዚህ ነብሰ-ገዳዮች የእያንዳንዱ ነብስ ዋጋ መክፈላቸው አይቀሬ ነው።
የቢሾፍቱው ግድያ የህወሃት “ጥልቅ ተሃድሶ” ጅማሬ መሆኑ ነው። ግን ህዝብን እየረገጡ ብዙ ሊዘልቁ አይችሉም። ፍም እሳት የሆነ የአመጽ ትውልድ ተፈጥሯል። እነሱ ባሰሩ እና በገደሉ ቁጥር ሚሊዮን ሆኖ የሚነሳ ትውልድ። ምንም ነገር ሳይዝ በድምጹ ብቻ የሚያስፈራ ትውልድ። ህዝብን ጠላት አድርጎ ለመግዛት የሚሞክር ስርዓት ይህንን ሁሉ ህዝብ ከቶውንም ገድሎ ሊጨርስ አይችልም።

Wednesday, October 5, 2016

ተቃውሞው ኣዲስ ኣበባ ፉሪና ኣለም ገና ገብቷል።



ተቃውሞው ኣዲስ ኣበባ ፉሪና ኣለም ገና ገብቷል።
#Ethiopia #EthiopiaProtests #AddisAbaba #MinilikSalsawi #Freedom
ፉሪ የጀመረው ተቃውሞ ወደ አለምገናም ቀጥሏል። ፉሪ ሱቆች፣ ካፌዎች፣ ባንኮች እና ባጠቃላይ መንገድ ዳር ያሉ ንግድ ቤቶች በጠቅላላ ዝግ ናቸው። ፉሪ መንገዱ ዳር እስከ ጆሞ ድረስ በታጠቁ የፌደራል እና የኦሮሚያን ዩኒፎርም የለበሱ ፓሊሶች በመንገዱ ፈሰዋል። ወጣቶች በየቅያሱ በየቅያሱ ተሰባስበው ይታያሉ። ባጃጅ እና ታክሲዎች የትራንስፓርት አገልግሎት እየሰጡ አይደለም። ጆሞ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቻቸውን በጊዜ ለቀው ቤተሰብ እየወሰዳቸው ነው። የትራንስፓርት እጥረቱ መሃል አዲስ አበባም ደርሷል። ሜክሲኮ ጋርም ከፍተኛ የታክሲ እጥረት አለ።
Image may contain: sky, cloud, outdoor and one or more people



የኢትዮጵያ ዉሎ – መስከረም 24 ቀን 2009 ዓ.ም #ግርማ_ካሳ

  



#AmharaResistance #OromoProtests #KonsoProptests #EthiopianProtests
መስከረም 22 ቀን 2009 ዓ.ም በቢሾፍቱ የተፈጸመው ኢሰብአዊ ጭፍጨፋን ተከትሎ በኢትዮጵያ በተለያዩ ቦታዎች ከፍተኛ ተቃዉሞዎች ተቀስቅሰዋል። ገዢው ፓርቲ “አዘነናል” ከማለት ዉጭ ምንም ሃላፊነት ያልወሰደ ሲሆን “የጥፋትና የአመጽ ሃይል በፌጠሩት ሁከት ዜጎች በመረጋገጥና ገደል ዉስጥ በመግባት ሞተዋል። የተተኮሰ ጥይት የለም” የሚል መግለጫ ነው የሰጠው። ተቃዉሞ ከተቀሰቀሰባቸው ቦታዎች መካከል የሚከተሉት በቀዳሚነት የሚጠቀሱ ናቸው፡
አዲስ አበባ
———
በአየር ጤና ፣ በጎጃም በረንዳ ፣ ወደ ቦሌ መስመር ተቃዉሞ፣ ካራ ቆሬ ተነስቶ ነበር። ተቃዉሞ ከአዲስ አበባ ዙሪያ ወደ አዲስ አበባ እየገባ ነው። እንደ መርካቶ ያሉ ቦታዎች ሱቆች በጊዜ ነበር የተዘጉት። የአገዛዙ ሜዲያ “በአዲስ አበባ ምንም ነገር አልተፈጠረም ፣ በአዲስ አበባ ተቃዉሞ ተነስቷል እያሉ በሶሻል ሜዲያ የሚያራግቢት የጥፋት ሃይሎች ናቸው” ይላል። የኦዲዮ፣ የቪዲዮ ፣ የመስል መረጃዎች በስፋት እየወጡ፣ በዚህ መልኩ አይን ያፈጠጠ ዉሸት መዋሽት ትልቅ ዝቅጠት ነው።
ጂማ
—-
የጂማ ዞን እስከአሁን በተደረጉ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች ብዙ ተቃዉሞ ያልተሰማባት ከተማ ነበረች። በኦሮሚያ አዳማ ቀጥሎ ትልቋ ከተማ ስትሆን ብዙ ብሄር ብሄረሰቦች በሰላም የሚኖሩባት ከተማ ናት። ወደ 45% የሚሆነው ነዋሪ አንደኛ ቋንቋ አፋን ኦሮሞ ሲሆን 55% አንደኛ ቋንቋዉ ከአፋን ኦሮሞ ሌላ ነው።
በጂማ በሚገኘው ትልቁ ዩኒቨርሲቲ ዛሬ በሕወሃት ዘመን ያልታየ ትልቅ ክስተት ነበር የተፈጸመው። ህወሃት በኦሮሚያ ያሉ ወገኖች አማርኛ እንዳይማሩ አድርጎ፣ በኦሮሞዉና በሌላው ማህበረሰብ መካከል መግባባት እንዳይኖር፣ መሰረታዊ የመብት ጥያቄዎችን በጋራ እንዳይጠይቁ ለማድረግ ችሎ ነበር። በዩኒቨርሲቲዎች የኦሮሞ ተማሪዎች ለብቻቸው ሌላው ለብቻው ነበር ህብረት የሚያደርገው። አይተማመኑም ነበር። ያም በዋናነት ሲጠቅም የነበረው አገዛዙን ነበር። በዚህ መልክ ተማሪዎችን በዘር ከፋፍሎ እርስ በርስ እያጋጨ በተለምዶ የሕዝብ ጥያቄ የሚንጸብረቅባቸው የትምህርት ተቋማትን ከጨዋታ ዉጭ ለማድረግ ችሎ ነበር።
ዛሬ ኦሮሞ፣ አማራ፣ ጉራጌ ሳይባባሉ በነቂስ በመዉጣት የጅማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ድምጻቸውን እስከ ማታ ድረስ ኢስያሰሙ ነበር”” መፈክሮችን እያቀባበልይ አንዴ በኦሮምኛ አንዴ በአማርኛ እያሰሙ ነበር በኦሮሞ፣ በአማራው በኮንሶ ወገኖች ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍን በደል ሲያወግዙና ሲቃወሙ የነበሩት።
በአዲስ አበባ ዙሪያ
—————-
– ከጀሞ ኮንድምኒየም አጠገብ የምትገኝ የኦሮምያ ሰፈር በተደጋጋሚ የመሳርያ ጩኸት ሲሰማ የነበረ ሲሆን ፖሊሶች ግርግሩን በመጠቀም ስማርት ሞባይሎች ከሕዝብ እየቀሙ ነው !! ምናልባትም ሰዎች መረጃ ፎቶ እንዳያነሱና እንዳይቀባበሉ ታስቦ ይሆናል !!! በፊሪ በተነሳው ታቃውሞ ምንም አይነት የወያኔ መኪና አያልፍም በማለታቸው የመሳርያ ድምፅ አልቆም ስላለ በጄሞ አካባብ ያሉት የግል ትምህርት ቤቶች ሰዓት ሳይደርስ ልጆቻችውን አውጡ ስላሉ፣ በጄሞ አካባብም ልጆቹን ለመውሰድ ቤተሰብ ሲሯሯጥ ነበር !! ከፍተኛ ወታደር የያዙ ተሸከርካሪዎች ወደ ጀሞ አቅጣጫ ሄደዋል።
– በሰበታ እና አለምገና የሚገኙ የስርዓቱ አካል ናቸው የተባሉ ኢንዱስትሪዎች ተቃጥለዋል። ፖሊሶች የህዝቡ ተጋድሎ ከአቅማቸው በላይ በመሆኑ ፈርተው የሸሹበት ሁኔታ ነው የነበረው።
– በአቃቂ አካባቢም የተኩስ ድምጽ ይሰማ ነበር።
– በቡራዩ ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ ተካሂዷል። አሸዋ ሜዳ ሁሉም ሱቆች ዝግ ነበሩ። ቦታውም በፌድራል ተወሮ ነበር። የታጠቅ ፋብሪካዎች ሰራተኞቻውን በጊዜ ነው የተበተኑት። ጉጄ አካባቢም እንደ አሸዋ ሜዳ ውጥረት ነግሶ ነበር። በርካታ የአገዛዙ ደጋፊዎች ንብረት ነው በተባሉ ላይ ዉድመት እንደነበረም ዘገባዎች ይጠቁማሉ። ባንኮፕች ተዘግተዋል። መኪና በከተማዋ አያልፍም።
ጎጃም
—–
– በጎጃም ኮሶበር – ዳሸን ቢራ ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ንብረትነቱ የኤፈርት የሆነ የጭነት መኪና በኮሱበር ጥቃት ደርሶበት ከጥቅም ዉጭ ሆኗል። በጭነት መኪናው የንመበሩት ቢራዎች መንገድ ላይ ሙሉ ለሙሉ ተደፍተዋል።
– ጎጃም መተከል (አሁን ወያኔዎች በቤኔሻንጉል ክልል ዉስጥ አደርገዉታል) በሚገኘው 23/45ኛው ወታደራዊ ካምፕ ይኖሩ የነበሩ ከ30 በላይ ወታደሮች የታጠቁትን ዘመናዊ መሳሪያ ይዘው ህዝባዊ ተጋድሎውን ለመቀላቀል ጫካ ገብተዋል። የመተከሉ 23/45ኛው ወታደራዊ ካምፕ ማለት በአማራ ተጋድሎ ወቅት ወጣቶች የተገደሉበት፤ አካለ ጎደሎ የሆኑበትና በስቃይ ርሃብና ጥም ውስጥ ደንጋይ እንዲፈልጡ ሲደረግብት የነበረ አካባቢ ነው። ወታደሮች ጫካ የገቡት ሌሊት ላይ የመሳሪያ መጋዘን በመስበር ከውስጥ የነበረውን በትንሹ 10 መትረጌየስና መሰል ዘመናዊ መሳሪያዎችን በመያዝ ነው። በዚህ የተነሳም መተከል ከፍተኛ የሆነ ፍለጋ ተጀምሯል።ፓትሮል በየጫካው ተጀምሯል። የወያኔ ደህንነቶችና ጀሌዎች እስከ ምሽቱ 2:30 ድረስ በግልገል በለስ ዞን አስተዳደር አዳራሽ ስብሰባ ላይ ነበሩ። ከወታደሮቹ በተጨማሪ በአማራ እና ኦሮሞ ላይ ወያኔ እየወሰደው ባለው ግድያ ሲበሳጩ ከነበሩ ወጣቶች መካከል ጥቂቶቹ ዛሬ ህዝባዊ ተጋድሎውን ተቀላቅለዋል።
– ጎጃም ሸርቆሌ አካባቢ ህዝብ ሊገድሉ የሄዱ 16 የወያኔ ወታደሮች ላይ ህዝቡ ራስን የመከላከል እርምጃ ወስዶባቸዋል። ሸርቆሌ አካባቢ የ12ኛ ክፍለ ጦር መገኛ ነው።
ምእራብ አርሲ፡
————
– በሻሸመኔ ላይ የኦሮሞና የትግሬ ወታደሮች ጎራ ለይተው እርስ በእርስ እየተታኮሱ እንደሆነ መረጃዎች እየወጡ ነው።
– በሻላ ወረዳ ተቃዉሞ ነበር። ህዝቡ የገዳንና የኦነግን ባንዲራ (ብዙዎች እንደ ኦነግ ባንዲራነት ሳይሆን እንደ ትግል አርማነት የሚያዩት) ሰቅለዋል።
ሰሜን ሸዋ፡ በአቦቴ ወረዳ ሰሜን ሸዋ ተቃዉሞ ነበር።
ምስራቅ ሸዋ
———-
– በዛሬው ዕለት በአዳማ የተነሳው ተቃውሞ ተከትሎ ብዙ የካድሬዎች የእርሻ ማሳ በእሳት ወድሞዋል አመፁ 40 ኪሎሜትር ድረስ እስከ አዋሽ መልካሳ ተስፋፍቶዋል። ከአዳማ አሰላ መንገድ ሙሉ በሙሉ ተዘግቶዋል።
– ማምሻዉን በአዳማ እየተደረገ በነበረው ህዝባዊ ተቃውሞ የአጋዚ ወታደር ተኩስ የከፈተ ሲሆን የኦሮምያ ክልል ፖሊስ ከተቃዋሚዎች ጎን ሆኖ ሕዝቡ ሲከላከል ነበር።፡እየተከላከለ ነው።
– በኑራ ሄራ ንብረትነቱ የአላሙዲን የሆነው የጥጥ ፋብሪካ በእሳት ተቃጥሏል። ወደ 20 የሚሆኑ የጭነት መኪናዎቹና ትራክተሮቹም እንደዚሁ።
– በመቂ በዝዋይ ተቃዉሞ ነበር።
ባሌ

ባሌ ሮቢ ምንም አይነት እንቅስቃሴ የለም። ሁሉም ነገር ተዘግቷል። አጋዚ ወአትደር ብቻ ነው በከተማዋ የሚራወጠው። የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት ሙሉ ለም ኡሉ ተዘግቷል።
ቦረና ዞን
——
በቡሌ ሆራ ወረዳ ሕዝቡ ከፍተኛ ተቃዉሞ አስነስቷል። ሁለት ሰዎች ሕይወታቸው ያለፈ ሲሆን ህዝቡ የወረዳዉን ፖሊስ ጣቢያ ፣ የአገዛዙ ጽ/ቤትን አዉድሟል። አድማ በታኞች መቆጣጠር ስላልቻሉ ሸሽተው ሄደዋል።

Tuesday, October 4, 2016

በሰማያዊ ፓርቲ ፅህፈት ቤት በወቅታዊ ጉዳዬችና በፓርቲው የወደፊት የስራ እንቅስቃሴ ዙርያ ከአባላት ጋር ዉይይት ተካሄደ፡፡



በሰማያዊ ፓርቲ ፅህፈት ቤት በወቅታዊ ጉዳዬችና በፓርቲው የወደፊት የስራ እንቅስቃሴ ዙርያ ከአባላት ጋር ዉይይት ተካሄደ፡፡
መስከረም 24 2009 ዓ/ም
Semayawi Party- Ethiopia's photo.
Semayawi Party- Ethiopia's photo.

በሰማያዊ ፓርቲ ፅህፈት ቤት በወቅታዊ ጉዳዬችና በፓርቲው የወደፊት የስራ እንቅስቃሴ ዙርያ ከአባላት ጋር ዉይይት ተካሄደ፡፡
መስከረም 24 2009 ዓ/ም

Monday, October 3, 2016

መቂ፣ ዝዋይ እና ሻሸመኔ ከባድ ተቃውሞ ተቀስቅሷል።  



ኢሬቻን ለማክበር የተጓዙ ሰላማዊ ዜጎች ላይ የደረሰው እልቂት ከተሰማ አንስቶ መቂ፣ ዝዋይ እና ሻሸመኔ ከባድ ተቃውሞ ተቀስቅሷል። ከትላንት ምሽት አንስቶ መንገዶች በተደጋጋሚ እየተዘጉ ነው። ተሽከርካሪዎች እየተቃጠሉ ነው። ህዝብ ወደ ጎዳና ወጥቶ ቁጣውን በምሬት እየገለፀ ነው ። #MinilikSalsawi
Minilik Salsawi's photo.
Minilik Salsawi's photo.