Sunday, September 25, 2016

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በስብሰባ ወቅት ምሁራኑን ሳቅ በሳቅ ያደረገና እንባ በእንባ ያራጩ ጥቂት ነገሮች



ሳቅ እና ለቅሶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
በስብሰባ ወቅት ምሁራኑን ሳቅ በሳቅ ያደረገና እንባ በእንባ ያራጩ ጥቂት ነገሮች እኒህ ነበሩ።
1 – አንዲት ሴት መምህርት ነች እጇን አወጣች እድሉን ስታገኝ “አሁን ወደ ስልጠናው ልገባ ስል ባለቤቴ ደውሎልኝ ነበር ‘ አደራሽን እናገራለሁ እንዳትይ እኔና ልጃችንን አስቢ አለኝ”….ሳቅ.. .በሳቅ…”ይሄዋ እርግጠኛ ነኝ ብዙዎቻችሁ እንደኔ ተብላችኋል”…ሌላ ሳቅ.. ይህኔ ክቡር ሰብሳቢው አቋርጠው “እረ ይሄ ፍርሃት ተደጋገመ ምንጬ ምን እንደሆን አልገባኝም? “ሴትዮዋ ተቀብላ” እንዴ አቶ ካሳ የምርዎን ነው? ምን እንደሚያስፈራን አያውቁም? ለነገሩ ህዝቡን አታውቁትም! ምን እንደሚያስደስተው እና እንደሚያስፈራው አታውቁም። ረጅም ጭብጨባ…!

2 – ሰብሳቢ ለተነሱት ጥያቄዎች ሲመልሱ ነገር ሲያረዝሙ ጊዜ መምህራኑ በጭብጨባ አቋረጡ ይህኔ “ባካችሁ 1 ደቂቃ ብቻ” አሁንም በጭብጨባ ተቋረጠ ሲጨንቃቸው ምን ቢሉ ጥሩ ነው? “እሽ በቃ የአይጥ መንገድ ብቻ ስጡኝና ልውጣ! “በልመና በአይጥ መንገድ ወጡ።

3 – ተናጋሪው የኩላሊት ህክምና ስፔሻሊስት ነው “እኔ ሀኪም እንጅ ፖለቲከኛ አይደለሁም። ግን አሁን አቶ ካሳ ሲናገሩ ‘እናየዋለን፣እናጠናዋለን ‘ብለዋል። የዛሬ 14 ዓመትም ነፍሳቸውን ይማርና የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስቴር አቶ መለስ እኔ ራሴ በተገኘሁበት ስብሰባ ላይ እንዲሁ ብሎ ነበር እና ዛሬም ከ14 ዓመት በኋላ እንደገና እናየዋለን፤ እንደገና እናጠናዋለን?” ስብሰባ ማዕከሉ በሳቅ ተወዛወዘ።

4 – ሰብሳቢው አቶ ካሳ ናቸው። ለተነሱት በርካታ ጥያቄዎች ሲመልሱ…ሰው ሲታገስ… ሲመልሱ..ሰው…ሲታገስ.መካከል ላይ ቦሌ አካባቢ ፎቆቹና ቪላዎቹ በአንድ ብሄር ጋንግስተሮች ተወሯል። ለሚለው ጥያቄ መልሱን ሲያብራሩ ..”ይሄን ነገር በደንብ ልንመረምረው ይገባል ፤ Rlly እንደተባለው ባንድ ብሄር ነው የሚለውን ልንፈትሸውና ልናጠናው…..” ..የሙህራኑ ሳቅ….እንጦጦ ድረስ ጮኸ።

5 – በጣም ወጣት ልጅ ነው እድሉን ሲያገኝ “ሌላ ዩኒቨርሲቲ ያሉ ጓደኞቼ በመናገራቸው ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው አውቃለሁ። ዝም ማለት ስላስላስቻለኝ እኔ ግን እናገራለሁ። ተናግሬ እንግዲህ የመጣውን ያው…..(ሰው በሳቅ)…እሽ ! ሰልፍ ይቻላል ተብሏል አዎ ለድጋፍ ሲሆን መኪና ተመድቦ፣ ክላሽ ተይዞ በፌዴራል ታጅቦ ይደረጋል። ችግሩ ህዝቡ ለመብቱ መሰለፍ ሲፈልግ ግን……” ምስኪን ይሄው ጥያቄው ማታ በኢቢሲ ተለቀቀለታ። እግዚኦ ነው ለቤተሰቡ
በመጨረሻም በቡድን ውይይት ወቅት(ስለ ትምህርት ጥራት ነበር ርዕሱ) አንድ ነፍሰ ጡር ሴት ተነስታ በሲቃ “ዛሬ ህዝብ እየሞተ የምን የትምህርት ጥራት ነው? ሁሉም የሚኖረው አገር ሰላም ሲሆን ነው። እኔ ለምሳሌ በዚህ ተቃውሞ ቤተሰቤን አጥቻለሁ (ሳግ እየተናነቃት) ዛሬ የስድስት ልጆች እናት የምትገደልበት፣ ልጇን ገድለው እላዩ ላይ ተቀመጭ የሚባልበት ጊዜ ላይ ተገኘን። ምነው ይሄ ታሪክ የሌላ በሆነልን፤ ምነው በሃገሬ ባይሆን ብየ ተመኘሁ ግን ሆኗል (ረጅም የሳግ ድምጽ) ሁሉም አንገቱን ደፋ፣ ግማሾቹ ዓይናቸውን በሶፍት ይጠርጉም ነበር።
ከዚህ በኋላ ነው የምሩ ሳታየር የተመለሰው መምህራኑ ስለ ሌላ አናወራም አገሪቱ ስላለችበት ወቅታዊ ሁኔታ ብቻ ነው በማለት።

፩ኛ – ጠ/ሚኒስትሩ ያወጁትን አዋጅ ባስቸኳይ ይመልሱ፤ ወታደሩም ወደ ቦታው ይመለስ!

፪ኛ – በየቦታው የሚፈጸሙት እስራት ፣ ቶርቸር እና አፈና ባስቸኳይ ይቁም!

፫ኛ – ለሁሉም መፍትሔው የስርዓት ለውጥ ነውና የስርዓት ለውጥ እንፈልጋለን። ይሄን ብቻ በዋናው መድረክ እንድታሰሙልን እንፈልጋለን።

ዋናው መድረክ ላይ ከሰዓት ሲቀርብ አወያይ ሆየ “በኛ ግሩፕ ከተነሱት የትምህርት ጥራት ችግሮች አንዱ ……..(divert እንዲህ ነዋ!)
 ኢዮብ ብርሃነ

የውሸትና የማስመሰል ጸብ በመቀሌ ተጀምሯል።የነ ኣባይ ወልዱ ኣንጃ ከተሸነፈ ሳሞራ ዮኑስ ሊባረሩ ወይም በጡረታ ሊሰናበቱ ይችላሉ የሚል ስጋት ኣለ



Amdom Gebreslasie's photo.
የነ ኣባይ ወልዱ ኣንጃ ከተሸነፈ ሳሞራ ዮኑስ ሊባረሩ ወይም በጡረታ ሊሰናበቱ ይችላሉ የሚል ስጋት ኣለ
የህወሓት “ጥልቅ ተሃድሶ”(ጥሎማለፍ) !
===========
የህወሓት ሁለቱ ኣንጃዎች ” በጥልቀት ለመታደስ” ተሰብስበዋል።
ለኣዲስ ኣበባው ኣንጃ “ኣቶ ኣባይ ወልዱ ከትግራይ ክልል ኣስተዳዳሪነታቸውና ከህወሓት ሊቀ መንበርነታቸው ማውረድ የሚል ኣላማ ኣንግበው መጥተዋል።

Amdom Gebreslasie's photo.
ይህ ማሳካት ማለት “በጥልቀት መታደስ” የሚል ትርጉም ይሰጡታል ይህ እውን ለማድረግ እንደመጡም እያስወሩ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ የመቐለው ኣንጃ የተፎካካሪው ኔትወርክ ኣፈራርሶ ስልጣኑ የበለጠ ሊያሰፋና ልእልናው ሊያስጠብቅ እየተጣጣረ ነው።
የመቐለው ኣንጃ ኣቶ ኣባይ በስልጣን ማቆየት፣ የኣዲስ ኣበባው ኣንጃ ስልጣን ማዳከም ማሳካት ማለት በጥልቅ መታደስ ነው።
የመቐለው ኣንጃ ዋነጃ ደጋፊ ጀነራል ሳሞራ ከመባረር(የነ ኣባይ ወልዱ ኣንጃ ከተሸነፈ ሳሞራ ዮኑስ ሊባረሩ ወይም በጡረታ ሊሰናበቱ ይችላሉ የሚል ስጋት ኣለ) ማዳን የሚል ግብም ለማሳካት እየታገለ ይገኛል።
Amdom Gebreslasie's photo.
የኣዲስ ኣበባው ኣንጃ ኣባይ ሲያወርድ ሊፈጠር የሚችል ግርግርና ኣለመግባባት ለማረጋጋት የሚለምኑና የሚሸመግሉ የድሮ የማእከላይ ኮሚቴ ኣባላት ከያሉበት ኣሰባስበው ኣሳትፈዋል።
የኣዲስ ኣበባው ኣንጃ ወቅታዊ ፕሮፖጋንዳ “ኣዲስ ኣበባው የኢህኣዴግ ግምገማ ኣባይ ወልዱና ገዱ ኣንዳርጋቸው ከስልጣን እንዲወርዱ ተወስነዋል በውሳኔው መሰረት ኣባይ በሌላ ኣመራር መተካት ብቻ ነው” የሚል ወሬ በመንዛት የኣባይ ወልዱ ከስልጣን መውረድ የማይቀር መሆኑ እየገለፁ ይገኛሉ።
Amdom Gebreslasie's photo.
የህወሓት በጥልቅ መታደስ ዓላማ ኣቦይ ስብሓት የተነጠቁት የበላይነት ማስመለስ፤ ኣቶ ኣባይ ወልዱ በኣጋጣሚ በእጃቸው የገባው ልዕልና ኣስጠብቆ መውጣት ከሚል ትርጉም የዘለለ ኣይደለም።
በህዝባችን ዓይን የዚህ ጥሎማለፍ (ጥልቅ ተሃድሶ) ውጤቱ “ጉልቻ ቢለዋወጥ ወጥ ኣይጣፍጥም” እንደሚባለው ፋይዳ ቢስ ነው።

«ኢልሜን ቦፋ ቦፋደቴ» ወይንም «የእባብ ልጅ እባብ» ያለው ጁኔይድ ሳዶ ሙሉ ታሪኩ እነሆ፤



«ኢልሜን ቦፋ ቦፋደቴ» ወይንም «የእባብ ልጅ እባብ» ያለው ጁኔይድ ሳዶ ሙሉ ታሪኩ እነሆ፤ Achamyeleh Tamiru
«ኢልሜን ቦፋ ቦፋደቴ» ወይንም «የእባብ ልጅ እባብ» ያለው የቀድሞው የኦሮምያ ክልል ፕሬዝደንት የነበረው ጁኔይድ ሳዶ ነው። ጁኔይድ ሳዶ «ኢልሜን ቦፋ ቦፋደቴ» ወይንም «የእባብ ልጅ እባብ» ያለው ያሁኑን የአማራ ትውልድ ነው። ሙሉ ታሪኩ እንደወረደ እነሆ፤
__________
<< «ኢልሜን ቦፋ ቦፋደቴ/የእባብ ልጅ እባብ» የሚለውን አቶ ጁነዲን ሳዶ ነበር ያሉት!!! ሰውየው ከኢህአዴግ ጋር በትልቅ የስልጣን ኮርቻ የነበሩና ዛሬ እራሳቸውን ከፓርቲው ያራቁ ወደተቃውሞም የገቡ ሊደነቁ የሚገባቸወ ናቸው። ቢሆንም ቅሉ ከመንግስት ጋር ተጣልቶ የሸሸ የድሮ ባለስልጣን ሁሉ እንደ ሀቀኛ መቁጠርና ማጀገን ግን ጅልነት ነው። የአቶ ጁነዲን ሳዶን ለአብነት እንይ ከዚህ ቀጥሎ የማወራላችሁ በጊዜው እዚያው ሰብሰባ ላይ በአካል ከነበረና የአቶ ጁነዲን ሳዶ ስም ሲነሳ እጅጉን የሚያመው አንድ ጓደኛየ ነው።
ጊዜው በ1997 ዓ.ም. የምርጫ ወቅት ነበር። አቶ ጁነዲን ሳዶ የኦሮሚያ ክልል ተወላጅ የሆኑትን የአዳማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ሰብስቦ ፖለቲካዊ ስብከት እያደረገ ነው። በሰብሰባው የነፍጠኛው ስርዓት በኦሮሞ ህዝብ ላይ ያደረሰው በደል፣ የነፍጠኛ ስርዓቱ የኦሮሞ ህዝብ ጠላትነት ብዙ ተሰበከ ከዚያም ለጥቆ አሁን ያሉት የነፍጠኛ ልጆችም ከአባቶቻቸው እንደማይለዩ እንደውም ተደራጅተው የነፍጠኛውን ሰርዓት ለመመለስ እየጣሩ እንዳሉና ይሀንን መፍቀድ አንደሌለባችው ብዙ ተባለ። በዚሁ ብዙ ሰው በስሜት ተናጠ። በመሀል አንድ ተማሪ ተነስቶ «ታድያ የዛሬ መቶ ዓመት የነበረን ነገር ካሁኑ ጋር እንዴት በቀጥታ ማገናኘት ይቻላል? እንዴት ያሁኑ የአማራ ተወላጆች ከዚያኛው ጋር በቀጥታ መገናኘት ተጠያቂም ማድረግ ይቻላል?” ብሎ ጠየቀ።
አቶ ጁነዲን ሳዶ የሰጡት መልስ እጅግ አሸማቃቂ ነበር። ቃል በቃል «ኢልሜን ቦፋ ቦፋደቴ/ የእባብ ልጅ እባብ» ነበር ያሉት። እጅግ አደገኛና መሰሪ አገላለፅ ነበር ያስፈራል! እንደነጁነዲን ሳዶ ዐይነቶች ጥላቻን የሚዘሩና ሌላ በርካታ በደል በህዝብ ላይ ያደረሱ ሰዎች ከመንግስት ጋር ተጣልተው መፅሐፍ ፅፈው ወይም በሌላ መልክ ተከስተው ይቅርታ ቢጠይቁ እንደኔ ተቀባይነት ያለው አይመስለኝም።>>
––––––––––
አቶ አሰፋን እጅግ እናመሰግናለን። ምንም እንኳ ሰውየውን የምናውቀው ብናውቀውም እሳቸው ደፍረው ይህንን የጁኔይድ ጉድ ባይነግሩን ኖሮ «የእባብ ልጅ እባብ» ብሎ እባብ ያደረገን ጁኔይድ ትናንት ወያኔ አላምጦ ስለተፋው ዛሬ እንደ እስስት መልኩን በመቀየር ህዝባዊ መስሎ የአዞ እንባ እያነባ የዋህ መስሎ ሊታይ «ቢሞክር ጅብ በማያውቀው አገር ሂዶ ቆርበት አንጥፉልኝ አለ» እንለዋለን።
የጋሽ አሰፋን ጽፉፍ ካነበብሁ በኋላ ጁኔይድ ትናንትና በአሜሪካ ድምጽ የአማርኛው ክፍል ያደረገውን ቃለ ምልልስ ካደመጥሁ በኋላ ዛሬ በሶስት ነገሮች ብቻ «ይቅርታ!» የጠየቀው ሰውዬ ትናንትና ያን ሁሉ አጥፍቶ ይቅርታው አልከበደውም ወይ ብዬ ትናንትና የተናገራቸውን ንግግሮች ፍለጋ ገባሁ። አንዱን ከታች ለጥፌዋለሁ። በዚህ ንግግሩ ውስጥ «ኢልሜን ቦፋ ቦፋደቴ/ የእባብ ልጅ እባብ» የሚለው ንግግሩ በኮድ ስም አለ። ወደ ድሮው ስርዓት ሊመልሱን ምናም የሚለው የኮድ ንግግር ነው። በዚህ የኮድ ንግግር ጁኔይድ እነ ልደቱን እያለ ያለው «ኢልሜን ቦፋ ቦፋደቴ» ወይም «የእባብ ልጅ እባብ» ነው።
ጁኔይድ ሳዶ ትናንትና በአሜሪካ ድምጽና በኦ.ኤም.ኤን የሰጠውን ላዳመጠ አሁን ይህንን ከታች ያተምሁትን ንግግር ከስድስት አመታት በፊት የተናገረው ነው ቢሉት ማን ያምናል? ይህንን ንግግር ይቅርታስ ያነጻዋል?



Saturday, September 24, 2016

አባሎቻችንና ሌሎች ዜጎች ከሕግ ውጭ እየታሰሩ ነው ሲል ሰማያዊ ፓርቲ ከሰሰ



አባሎቻችንና ሌሎች ዜጎች ከሕግ ውጭ እየታሰሩ ነው ሲል ሰማያዊ ፓርቲ ከሰሰ
በመላው ሀገሪቱ የሰማያዊ ፓርቲ አባሎችና ሌሎችም ዜጎች ከሕግ ውጭ በሆነ አያያዝ በገፍ እየታሰሩ መሆናቸውን የሰማያዊ ፓርቲ ፕሬዝዳንት ተናገሩ።
በተመሳሳይ ሁኔታ ከ20 የማያንሱ ዜጎች ከሕግ ውጭ በምዕራብ ኦሮምያ በጅማ ገነት ወረዳ መታሰራቸውን አንድ የተቃዋሚ ፓርቲ ወኪል ገለጹ።
ከመንግሥት በጉዳዩ ላይ ለጊዜው ማብራርያ ለማግኘት አልተቻለም።
በኦሮምያና በአማራ ክልሎች የተቃውሞ ሰልፎች መካየድ ከጀመሩ በኃላ በአጠቃላይ በሀገሪቱ ውስጥ በዜጎች ላይ እየተካሄዱ ነው ያሉት የአፈና እርምጃዎች እየተባባሰ መሆኑን በመግለጽ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀ መንበር አቶ ይልቃል ጌትነት መንግሥትን ከሰዋል።
ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ። http://av.voanews.com/clips/VAM/2016/09/23/7d0edaac-75aa-4c66-9b40-d0e20479a612.mp3
Vm
P

ፋይል- የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀ-መንበር አቶ ይልቃል ጌትነት

የኢትዮጵያ ሕዝብ በትግሉ ኣምባገነንና ኣሮጌ ስርዓቶችን ለማስወገድ ኣዲስ ኣይደለም። ሕወሓት መራሹን ኣገዛዝ እስካልጣልን ዘንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሰላምና ነጻነት አናገኝም።



ሕዝቤ ሆይ :- ሕወሓት መራሹን ኣገዛዝ እስካልጣልን ዘንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሰላምና ነጻነት አናገኝም። የኢትዮጵያ ሕዝብ በትግሉ ኣምባገነንና ኣሮጌ ስርዓቶችን ለማስወገድ ኣዲስ ኣይደለም።
Image may contain: 3 people , text
ሕዝቤ ሆይ :- ሕወሓት መራሹን ኣገዛዝ እስካልጣልን ዘንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሰላምና ነጻነት አናገኝም።
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – ሕወሓት ወንጀለኛ ነው። ነጋሪ ኣንፈልግም። አሁን የሚያስፈልገው ሕዝቡን በጋራ ኣያይዞ ሕወሓት የሚባለውን ማፊያ መሰሪ በቀለኛ ጸረ ሰላምና ጸ ሕዝብ ሰው በላ ኣገዛዝ ማስወገድ ብቻና ብቻ ነው። ለዚህም ነው የስርዓት ለውጥ ያስፈልጋል ብለን እየጮኽን ያለው።ለዚህም ነው ሕዝባዊ መንግስት ያስፈልጋል ብለን እየጮኽን ያለነው።ለዚህም ነው በዘርና በመንደር መቧደን ቆሞ በጋራ የሕዝቦች እኩልነት የተረጋገጠባት ኢትዮጵያ ትመስረት እያልን የምንጮኸው።ለዚህም ነው በኣንድነት በባንድራ በሃገር ወዳድነት ሽፋን ሕዝብ እንዳይረገጥ በጩኸት በማስፈራራት ከኛ በላይ ላሳር የሚል ስሜታዊ የጡዘት ፖለቲካ ይቁም እያልን ኣምባገነነኦችን ለሜጣል ላሌመፍጠርም እየታገልን ያለነው። ለዚህም ነው ኢትዮጵያውያን በመላው ሃገሪቱ ተዘዋውረው የመስራት መብታቸው ይከበት ብሌን የምንታገለው።ለዚህም ነው ግድያና እስር ቆሞ በመከባበርና በመቻቻል ፖለቲካ ኣገር ትመራ ብለን የምንጮኸው በኣጠቃላይ ለሕዝብ ነጻነትና መብት መከበር ስኬት ለፖለቲካና ኢኮኖሚ ሰላም መረጋገጥ ሕወሓት መወገድ ኣለበት።
የኢትዮጵያ ሕዝብ በትግሉ ኣምባገነንና ኣሮጌ ስርዓቶችን ለማስወገድ ኣዲስ ኣይደለም። በደሃው ገበሬ ላብ ሲኖር የነበረውን የጥቂት መሳፍንቶችና የራስ ተፈሪ መኮንንን ፊውዳላዊ ጨካኝ የሆነ ኣገዛዝ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዳር እስከዳር በመንቀሳቀስ ራሱን ንጉስ ኣድርጎ የሾመውን ኣገዛዝ ያስወገደ ቢሆንም በጣልቃ ገብነት የመጡት ወታደራዊ መኮንኖችም ለሃገርና ለወገን ይጠቅማሉ የተባሉ ዜጎችን ደም በመጠጣት በማሰር በማሳደድ ታሪክ ይቅር የማይለው ግፍ በመስራት በሃገር ኣንድነትና በባንድራ ሽፋን በግዳጅ ወጣቱን ለስልጣናቸው ማቆያ በመማገድ ሲተጉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዝም ብሎ ኣላየም በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች በተከፈሉ መስዋትነቶች ደርግ ላይነሳ የተንኮታኮተ ሲሆን ይህን ተከትሎ ስልጣን ላይ የወጡት ዘረኛ ዘራፊ መንደርተኛ ተሳዳቢ ገዳይ እጅግ ጨካኝና በመሳሪያ ብቻ የሚተማመኑ የሕወሓት ኣምባገነን ኣመራሮች ስልጣኑን ተቆጣጥረው በዲሞክራሲና በልማት ሽፋን ሕዝቦችን ለከፍተኛ ሰቆቃ ከመዳረጋቸውም በላይ ኢትዮጵያ በዘመኗ ተፈራርቀው የነበሩ መንግስታት ያልሰሩትን ወንጀሎች በሕወሓት እየተሰሩ ታሪክ ይቅር የማይለው ግፍ በዘረኞች እየተፈጸመ ነው።
ስለዚህ እነዚህም ጨካኖች በሰለጠነ ዘመን ያልሰለጠኑ ዘረኞችን ተባብረን ማስወገድና ለመጭው ትውልድ መብት ነጻነት እና እኩልነት የተረጋገጠባትን ኢትዮጵያ ለማስረከብ የዜግነት ድርሻችንን እንወጣ። #ምንሊክሳልሳዊ

Friday, September 23, 2016

የትግራይ ወያኔ ሌባ ነው የሚለው የኢቶዮጵያ ህዝብ እዉነታነቱን እራሱ ወያኔ በድጋሜ መሰከረ

  


የትግራይ ወያኔ ሌባ ነው የሚለው የኢቶዮጵያ ህዝብ እዉነታነቱን እራሱ ወያኔ በድጋሜ መሰከረ
——————————————————————-
ባለፈው ወር አካባቢ ወያኔ ባወጣው የልሳኑ መግለጫ በስልጣን ላይ ያሉ አባላት ስልጣናቸዉን መከታ በማድረግ ህዝብን ከማገልገል ይልቅ የግል ጥቅማቸዉን በማሳደድ ሃገርን መዝረፍ ስራየ ብለው ይዘዋል ብሎ በግልጽ ወያኔ የሌባ ድርጅት መሆኑን ለኢትዮጵያ ህዝብ ተናገረ። አሁንም እንደገና በ ፩፱፱፰ (1998) አመተ ምህረት አሳትሞ ትምህርት ሲያስተምርበት የነበሩት መጽሃፎች የሃገሪቱን የተለያዩ ክልሎችን በተለይ የአማራዉን ክልል ዙሪያዉን ተቀራምተው አሳንሰው በመሳል በትክክል ያላስቀመጠና ትልቁን የኢትዮጵያን ራስ ደጀን ተራራርን ከጎንደር አዉጥተው ትግራይ ዉስጥ ነው ብለው ለአመታት ሲያስተምር እንደነበርና ይህ በስተት መሆኑን ይቅርታ እንጠይቃለን መጽሃፎቹንም አስተካክለን ልከናል አሉ። ይህ አይደለም ሌባ ማለት? ይሀን ያህል አመታት እንዴትስ ሆኖ ነው መምህራኖች ይሀን ሲያስተምሩት የነበሩት፤ ራስ ደጀን ትግራይ ዉስጥ ነው ብሎ ማስተማር? በመምህርነት የሰለጠነ ሰው ዉሸትን እንደ እዉነት አምኖ እንዴት ይሀን ያህል አመታት ያስተምራል? ምንስ አይነት መምህር ነው? የትግራይ ዋና ከተማ ደደቢት ነው ብሎ የተጻፈዉን መጽሃፍ እንዴት ነው አስተማሪው ይሀን ከማስተማሩ በፊት ይህ ነግር እዉነት አይደለም ብሎ መጠየቅ የማይችለው? ነው ወይስ ደደቢት የትግራይ ዋና ከተማ መሆኑን ወይም አለመሆኑን አያዉቅም ወይም እንዲሆን ስለሚመን ዝም ብሎ የተጻፈዉን ዉሸት ያስተምራል? እኔ የሂሳብ አስተማሪ ነኝ፤ እንዴት ሆኖ ነው መጽሃፍ ላይ ፩+፪ = ፩፪ ባገኘው ይህ ትክክል ነው ብየ ዉሸትን እያስተማርኩ ሂሳብ አስተማሪ ነኝ የምለው? ትምህርቱስ እንዴት ነው የሂሳብ ትምህርት የሚባለው ተማሪዉስ ምን አይነት ነው ይችን ትንሽ ነገር እንኳን ስህተት መሆኑን ማየት የማይችለውና ስህተት መሆኑን ለመናገር የማይሞክረው? ሂሳብ እዉነትን የምናረጋግጥበት የጥናት መስክ እንጅ ዉሸትን የምንማርበት አይደለም ። ማነው ነው ተጠያቂዉ ይሀን ዉሽት ተምሬአለሁ ብሎ ይዞ ወጥቶ ሃገርን በዉሸት የሚያምስና የሚያበጣብጥ እንደነ መለስ ዜናዊና የወያኔ ቁጭበሉወች? ለዚህ ነው ወያኔ ሌባ እያለ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚናገረዉና የወያኔን ትክክለኛ ባህሪ የሚገልጸው ። የትግራይ ወያኔ የራሱ ያልሆነን ነገር በመዝረፍ የራሱ በማድረግ ሃብትና ንብረት ማግበስበ ሞያው ነው አሁን እንደታየው የንብረቱ ባለቤቶቹ አምርረው ከጠየቁ በስተት ነው ብሎ መመለስ ነው። አሁንም ወልቃይት ጠገዴ፤ራያ፤መተከል ሁሉም ወደ አማራው መልሰናል ይቅርታ በስህተት ነው ይህ ሁሉ ወንጀል በደልና ግፍ የፈጸምነው ብለው ብቅ ይሉ ይሆናል፤ ግን አሁን ያን ማድረጉ ጅብ ከሄደ ዉሻ ጮሀ ነው፤ ከብዙ ወንጀል በኋላ ዘግይቶ የመጣ መፍትሄ መፍትሄ ሳይሆን ራስን ለማዳን የሚደረግ ጥረት ነው፤ በዚህም ምክንያት እርምጃው ተገዶ የሰዉን ንብረት መመለሰ ብቻ ሳይሆን ለዘረፋ ለአድሎ ለግድያና ግፍ መፈጸሚያ መሳሪያ ያደረገውን ስልጣኑን እንዲለቅና ፍትሃዊ እርምጃን ለመቀበል ዝግጁ መሆን ብቻ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ በሌባ መታሰር፤ መገደል፤ መዘረፍና ሌቦች በቅንጦት እየኖሩ የንበርቱ ባለቤት የሆነው ህዝብ ግን በድህነት ብግፍ በስራትና ብግድያ የሚኖርበት ዘመን ማቆም አለበት፤ የህዝቡም ጥያቄና ተጋድሎ ይሀንን እዉን ለማድረግ ብቻ ነው።

መስከረም 11—2009 ዓ/ም— በደ/ብርሃን ዩኒቨርስቲ የአድሀሪው ወያኔ መድረክ መሪዎች በእምባ ሲራጩ የዋሉበት ቀን




Bilderesultat for debre berhan university






መስከረም 11—2009 ዓ/ም— በደ/ብርሃን ዩኒቨርስቲ የአድሀሪው ወያኔ መድረክ መሪዎች በእምባ ሲራጩ የዋሉበት ቀን 3ኛ ቀኑን ያስቆጠረው የወያኔ የከፍተኛ ት/ት ተቋማት ምሁራንና ሰራተኞችን አትኩሮት የማስቀየስ የውይይት መድረክ ዛሬ ብዙዎችን በእምባ ሲያራጭ ውሏል።
በተለይም በደ/ብርሃን ዪኒቨርስቲ በወያኔ ካድሪዎችና አጎብጓቢዎች የተመራው መድረክ ሳያምኑበትና ውስጣቸው ሳይቀበለው በአረመኔዎቹ የድርጅቱ ከኛ በላይ ላሳር ባዮች የተሰጣቸውን ተልዕኮ በዪኒቨርስቲው ማህበረሰብ ላይ ለመጫን የሚሞክሩትን የመድረኩመሪዎቹን ሳይቀር አስለቅሷል።
ነገሩ እንዲህ ነው በዪኒቨርስቲው የተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ስር በተማሪዎች መኝታ ቤት ኦፊሰርነት የምትሰራው ወጣት መልካም በአማራነቷ የምትኮራ በትውልዷ ጎጃሜ ናት።ሆኖም ይህን እንዝህላል መንግስት/መንግስት ስለው ይከብደኛል ይህን የደደብ ራስ ወዳዶች የዘራፊ ባንዳዎች ጥርቅም/ተቃውመው የህብረተሰቡን ጥያቄ አንግበው ወደ አደባባዮች የወጡ 4 ወንድሞቿ 4 የአጎቶቿ ልጆች በድምሩ 8 የቤተሰቧ አባላት የደረሱበት አልታወቀም።
ይህንንናሌሎች መብታቸውን ለመጠየቅ በሚል ወደ አደባባይ ወጥተው የነበሩ የህዝብ ልጆች በህዝብ ደም በደነደነው ወያኔ ሰለባ መሆናቸውን ጠቅሳ ፍረዱኝ ቤተሰቦቼን መልሱልኝ ፍትህ ለኢትዮጵያ ህዝብ ማለቷ ነበር መላውን ተሰብሳቢ በእንባ ያራጨው። መድረኩን ሲመሩ የነበሩት የዩኒቨርስቲው ፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ባዪ ጌታሁን እና የጤና ኢንስቲቲዪት ዳይሬክተርና መምህሯ ወይዘሮ ሶደሬም ሲቃ እየተነነቃቸው የእንባ ዘለላ ከፊታቸው ዱብ ዱብ ሲል ታይተዋል።
ከ110 በላይ ተሰብሳቢዎችን ሲመሩ የነበሩት እነዚሁ ሰዎችም መሪ ተብዬው ደንባራው ኃ/ማሪያም/ስሙን ሞት ይጥራውና/በግብታዊነት የተናገረውን የእርምጃ ይወሰድ ትዕዛዝ ከማውገዝም በሻገር አንቀበለውም እኛም አናምንበትም ሲሉ አቋማቸውን አሳውቀዋል።
የኢትዮጵያውያን ደም መቼም ደመ ከልብ ሆኖ አይቀርም!!! እንዋጋለን በዳዮቻችንን እንፋረዳለን!!! ትግሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!! ድል ለሰፊው የሃገሬ ህዝብ!!!